Truth be told, when I used to come across your message, even without cosindering what you have to say, just because you were aganist this so called movement, I ignored it. Looking back now, after God opened my eyes, had I heed the message you were relaying, It would have saved me so many heartache, not to mention the time I wasted with these fools, instead of growing in knowledge and wisdom of Christ. I thank God through Jesus Christ, for giving us brothers like you, especially for Ethiopian evangelical church, whom, by all counts have lost in defending the Gospel. Him and the Scripture alone is suffice for Godly life, which we are called to live. May the Lord bless you and keep you safe!
ስለ ምታስተምረው ትምህርት እግዚአብሔር አምላክ ይባርክህ። ዛሬ ዋጋ ቢያሳጡህም እንኳ፤ በመጨረሻ ጊዜ ዋጋህን ከእግዚአብሔር እጅ ትቀበላለህ።
ወንድም ዘላለም፣ 1ኛ ቆሮ 13 ላይ ያለው ስለመንፈሳዊ ብስለት ነው ባልከው ሀሳብ አልስማማም። ምክንያቱም እነዚያ ጸጋ በነበሩበት ጊዜ የበሰሉት አማኞች ላይ(ሐዋርያት ላይ) በብዛት ታየ እንጂ አልተሻረም ነበር። ጊታ ሲመጣ ነው የሚለውም ሀሳብ አያስኬድም አንተ ካቀረብከው ተጨማሪ ምክንያት እዚያው ክፍል ቁጥር 13 ላይ አለ "እንዲህም ከሆነ፥ እምነት ተስፋ ፍቅር እነዚህ ሦስቱ ጸንተው ይኖራሉ፤ ከእነዚህም የሚበልጠው ፍቅር ነው።" ጌታ ከመጣ በኋላ ተስፋ የሚባል ነገር አይኖርም፣ ሁሉም የሚታይ ስለሆነ ።በታሪክም እንደምታውቀው ደግሞ ከሐዋርያው ዮሐንስ እልፈት በኋላ እነዚህ ጸጋዎች አሉ ብለው የተነሱ ቡድኖች በሙሉ ሀሰተኖች ናቸው።
ነብይም ትንቢትም ፈዋሽም ልሳንም የለም አራት ነጥብ ጌታ ብቻውን አሁንም ይፈውሳል። ማንም ጣልቃ ያልገባበትና ማንም ያልከበረበት ፣ ነገር ግን ጌታ ብቻውን የከበረበት ፈውስ በቤቴ ያየሁ አማኝ ስለሆንኩ ስለዚህ እውነተኛ ፈውስ እመሰክራለሁ ። ፈዋሽ ተንባይና ሃዋርያ የተባሉት "የዚህ አገልግሎት ባለ ራዕይ የቸርቹ መስራችና ባለቤት ነኝ" ብለው ራሳቸውን ያስተዋውቃሉ ። በዝች አለት ላይ ቤተክርስቲያኔን እሰራታለሁ ያለ ፣ የቤተክርስቲያን መሠረት የሆነና ራስ የሆነ አንድ ነው ። እሱም ጌታ ኢየሱስ ይባላል።
ጴንጤነት በአንድ ጥቅስ ላይ የተመሰረተ ስለሆነ ፣ በልሳን የማይናገሩ አማኞችን "በመንፈስ ቅዱስ የማያምኑ በአብና በወልድ ብቻ የሚያምኑ ይሏቸዋል"
ይሄ ነው እንግዲህ "ዕውቀት"
በአማርኛ ፎንት ብዙ መፃፍ ቢቻል ብዙ የምለው ነበረኝ ።
ነብይም፣ ትንቢትም፣ ፈዋሽም፣ ልሳንም አሉ። እነዚህ ስጦታዎች ለመቋረጣቸው ምንም መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ የለም።
@@ignitus7777 ወዳጄ ያለ ነብይና ትንቢት በቅድስና መኖር አይቻልም?
ነብዩ የተፈለገው ፣ ስልክ ቁጥሬን እንዲነግረኝ ነው ወይስ ፎቅ ትገነባለህ ፣ አሜሪካ ትበራለህ ብሎ አንዲነግረኝ?
እስኪ በነብይና በትንቢት አማኝ ከሆንክ ፣ ነብዩ "ያለህን በሙሉ ሸጠህ ለድሆች ስጥ ይልሃል ጌታ" ቢልህ ፣ ታደርገዋለህ?
ሌላ ምሳሌ ልስጥህ ፣ በአሜሪካ ፣ በካናዳ ፣ በዩሮፕ ባደጉ አገሮች ላይ ብዙ የኢትዮጵያውያን ቸርቾች አሉ ፣ ለምንድነው በአንዱም ቸርች ነብይ ሃዋርያ ምናምን የሚባል ነገር የሌለው? ሃብታም አገር ላይ ስለሚኖሩ ነው እግዚአብሔር ለነሱ ነብያትን የከለከላቸው?
በኢትዮጵያ ከደቡብ ክልል የተነሱ ነብያት በሙሉ አጭበርባሪዎች ናቸው። በአፍሪካም የሚነሱ ነብያት እንደዛው።
ጌታህን ማስደሰት ትፈልጋለህ? በእምነትና በቅድስና ኑር። ነብይ መጥቶ "ወንድምህን ይቅር በለው ወይም ደሃን እርዳ ይልሃል ጌታ" እስኪልህ ድረስ አትጠብቅ ፣ ቃሉ ብቻውን ሙሉ ነው ይበቃሃል።
@@yfantaye3977 እነዚህ የጸጋ ስጦታዎች በኤፌሶን 4 እንደገለጸው ለቤተክርስቲያን መታነጽ የተሰጡ ናቸው። የማይገናኝ ነገር አትጥቀስ።
@@yfantaye3977 የትንቢት አስፈላጊነት የጌታን ቃል አስፈላጊነት ለመሙላት አልተሰጠም። ደግሞ አሁን አንተ በምትለው አባባል ከሄድን ከጅምሩ ጌታ ያ ጸጋ ሳያስፈልግ ነው የሰጠው ማለት ነው። እግዚአብሔር ሃሳቡ አይቀየርም፤ ያኔ በነብያት ሰርቶ አሁን እነሱ ይቅሩ ብሎ ውሳኔውን አይቀይርም።
@@yfantaye3977 በውጭ ሀገር ያሉም የኛ ቸርቾች ውስጥ ነብያት አሉ።
ጋሽ ዘሌ ገጠር ስለነበርኩኝ ወዲያው አላየሁኝም። ሴሴሽንስቶች ለይተህ ያቀረብክበትን መንገድ እና አንተ ራስህ ከእነርሱ የምልከታ በማሳየት ፈውሰና የመንፈሳዊ ወይም የፀጋ ስጦታ ያለመቋረጡን ደግሞ ግን ፈውስ በፈቃዴ እግዚአብሔር የሚሆን እንጂ እንዲሁ በመዳ እንደ አገራችን የፈውስ ቸርቻሪ ነቢያት አንፃር እንዳልሆነም የገለፅክበትንም መንገድ ወድጀዋለሁኝ። ስለዚህ ከቅቡልነት አንፃር አንዳንድ ሴሴሽንስቶች በሚል ያለ ገለፃ በfb ገጽህ ላይ የተቀመጠበትን መንገድ በዚህ መልኩ መብራራቱ ጥሩ ነው። መግለጫህንም ቀድሞ ካየሁበት እይታ ላይ እንድፀናም የሚያደርግ ነውና ወድጀዋለሁኝ። ቀጣዩንም ለማዬት ቸር ያሰንብተን።🙏🙏🙏
ጸጋ ይብዛልህ
በመጀመሪያ ምልክትና ተዓምራት ዋና ዓላማው እግዚአብሔር ከቤተክርስቲያን ጋር ለመሆኑ ወይም የሚሰበከው ወንጌል ከእግዚአብሔር ለመሆኑ ማረጋገጫ ለመስጠት እንደሆነ መታወቅ አለበት። አይደለም በዚህ ብዙ አሳቾች (እናንተንም ይጨምራል) ባለበት ይቅርና በመጀመሪያ ዘመን ላይ የነበረችው ራሷ ይህ የእግዚአብሔር ምስክርነት አስፈልጓት ነበር፤ ክርስቶስ ራሱ ይህ የእግዚአብሔር ማረጋገጫ አስፈልጎት ነበር።
በከፊል በጣም ጥሩ ማብራሪያ ነው። ሆኖም ብታስብበት ብዬ ከማስባቸው ውስጥ የሚከተለው ይገኝበታል። 1ቆሮ 1:7 ላይ እኮ "አንድ የፀጋ ስጦታ አይጎድልባችሁም" የተባለው ምዕራፍ 12-14 ስላሉት መንፈሳዊ ስጦታዎች አይደለም። አውዱን ከተመለከትን በክርስቶስ በማመን ምክንያት ስለሚገኝ የአምላክ ስጦታ ነው ሚናገረው (ለምሳሌ የደኅንነት ስጦታ (ኤፌሶን 2:8-9))። ይህ ስጦታ አይጎድልባችሁም ማለት የተሰጡን ስጦታዎች (ፅድቅ፣ ሰላም፣ መዳን እና የዘላለም ሕይወት) እንደማይጎድሉብን የተሰጠ ዋስትና ነው።
ወንድሜ ፈረንጆች እንደሚሉት loser ነህ፡ ሴሴሽንዝም ቃለ ሕይወት እና መካነ ኢየሱስ ራሱ ሲያራምዱት የነበረ ትምህርት እና መንፈስ ቅዱስ ጣልቃ በመግባት እንደ አንተ በክርክር ሳይሆን በተግባር እያሳየ አቋማቸውን አስለውጧቸዋል፡ ዛሬ አንተ እንደ አዲስ ማብራራት ትፈልጋለህ ፡ ወንድሜ አትድከም ቲኦሎጂካሊም ሆነ ፕራክቲካሊ ሴሴሽንዝም ትክክል አይደለም ፡ እሺ በፊት ሴሴሽንዝም የቤተ እምነቶችና የአስተምሮ መለያ ነበር ፡ አሁን አንተ ስለ ሴሴሽንዝም የምትነግረን ልሳን እንድንተው፡ ትንቢት እና ፈውስን እንድንተው ነው ? የስህተት ልምምዶች እና አስተምሮዎችን ለምን ትቀላቅላለህ፡ ሌላው አንድ ሰው በነቢያት ተከፍሎት ነው የፃፈው ብለሃል ፡ አንተ እየተከፈለህ ነው ማለት ነው የምትፅፈው?
More grace to you brother 🙏 thanks!
ዘሌ ኣንተ በኣንድ ወቅት ካልቪኒስት ነኝ ብለህ ነበር ታድያ ዪሄ ኣስተምህሮኮ ሁሉም ነገር ኣስቀድሞ የተወሰነ(predestined/decreed)የሆነ ነው ሃሳባችን መረዳታችን ጭምር።ስለዚ ካልቪንስት ሁነህ ምን ኣድርጉ ነው ምትላቸው።
Brother predestined malet mn endahona badnb alteradahem man endatawesene manm ayawekem egna hulem lebegoch ejig eyatateren meserat alaben leemsale ene gash zelalalemen ekawem nber segabagn gn esamachw jemerku ayah bzu begoch ewnatun balamawek midanageru alu pawlos endalew letemeretut enetegaln
Stay blessed and move forward!
ወንጌል ማርቆስ 16:16
ዘሌ ይህን ትምህርት መጽሐፍ ቅዱሳዊ አይደለም
✝እግዚአብሔር ፡ ይባርክህ ።
ፈውስ ✝እግዚአብሔር ሲፈቅድና ፈቃድህ ቢሆን ተብሎ ሲጸለይ የሚሆን ነው እንጂ በኛ ንግግር ብቻ አይሆንም ።
on this subject matter you are completely mistaken. (Kalehiywet church teaching).
በረታ ወንድሜ ጌታ ጸጋውን ያብዛልህ የማንቀከያ የመለከት ድምጽ ሆነሀል እና ለትውልዱ
Truth be told, when I used to come across your message, even without cosindering what you have to say, just because you were aganist this so called movement, I ignored it. Looking back now, after God opened my eyes, had I heed the message you were relaying, It would have saved me so many heartache, not to mention the time I wasted with these fools, instead of growing in knowledge and wisdom of Christ. I thank God through Jesus Christ, for giving us brothers like you, especially for Ethiopian evangelical church, whom, by all counts have lost in defending the Gospel. Him and the Scripture alone is suffice for Godly life, which we are called to live. May the Lord bless you and keep you safe!
በሁለተኛ ደረጃ በተለያየ ሰንካላ ሰበብ ዕምነተ ጎደሎዎች በእግዚአብሔር እውነት ላይ እና በህያው ቤተ ክርስቲያን ላይ ሲሳለቁ እውነት ስላላቸው አትንኳቸው ማለትህ አንተም ከነሱ አንዱ ለመሆንህ ማስረጃ ነው። የናንተ ዕምነተ ጎዶሎነት የእግዚአብሔርን እውነት አይለውጥም፡፡
የናንተ አገልግሎት በመጀመሪያው ዘመን ወደ ቤተ ክርስቲያን ሰርገው ከገቡ ፈሪሳውያን ቢብስ እንጂ አያንስም። ስውር አጀንዳችሁ ህያው ቤተ ክርስቲያንን የማፍረስ እንደሆነ በብዙ መንገድ ተገልጧል። አሁን ጭንብላችሁ እየተገለጠ በመሆኑ ብዙዎች ማንነታችሁን እየተረዱ ነው።
ምን ለማለት ፈልገህ ነው?
Ende prophet neh ende😅
ግልጽ መልክት እግዚአብሄር ይባርክህ ጋሽ ዘሌ።
አክባሪህ ነኝ ዘላለም።
"መንፈስ ቅዱስ እና ካሪዝማዊ ቀውሶች" የሚለውን መጽሐፍህን በአጋጣሚ አግኝቼ ገዝቼ እያነበብኩ አልጨረስኩትም ነበር እና... ከመንገድ ስመለስ ሌሎች መጻህፍትን ከያዘ ቦርሳዬ ጋር ተሰረቅኩኝ እና ቅጂውን ላገኝ የምችልበት መንገድ ይኖር ይሆንን?
እዚህ ይገኛል። በነጻ ማውረድም ይቻላል።
www.good-amharic-books.com/library?id=107
ወይም ከቴሌግራም ገጼ በአንድ ሙሉ ቅጽ ለማግኘት፤
t.me/zelalemmengistu/647
@@zelalemmengistu2 አመሰግናለሁ፤ መበርታትንም ካንተ በብዙ እያስተማርከኝ ነው ብዬ አምናለሁ። ተባረክ!
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏😭😭😭😭😭😭😭😭😭🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🙌🙌🙌🙌🙌🙌🙌🙌🙌
Awesome point, thanks 🙏 brother Zele
Kemetsihafu mekuaretachewn myasay tiks ale
ሰላም ጋሽ ዘሌ
አነጋገሩ ሁሉ ደስ አይልም ነገረኛ መሆኑ በደንብ ያስታውቅበታል ፣ ብራዘር እግዚአብሔር ፍቅር ነው ስህተትን አታርም ( አቅሙና ፀጋው ካለህ) ማለት ሳይሆን ነገር ግን ሰውን ሳትወድ እግዚአብሔርን መውደድ አትችልም! ኦራማይ
Focus on the message and compare where our churches are standing
ጋሽ ዘሌ እንኳን በሰላም መጣህ።
Sew mesay
Weregna, hasab kaleh yetenagerewen ende egziabeher kal mogete. Sedeb mendenew?
ዘሌ ኣንተ በኣንድ ወቅት ካልቪኒስት ነኝ ብለህ ነበር ታድያ ዪሄ ኣስተምህሮኮ ሁሉም ነገር ኣስቀድሞ የተወሰነ(predestined/decreed)የሆነ ነው ሃሳባችን መረዳታችን ጭምር።ስለዚ ካልቪንስት ሁነህ ምን ኣድርጉ ነው ምትላቸው።
የጴንጤ ትምህርት የሀሰተ ትምህርት ነዉ ምንም ክርሰቶሳዉይ አይደለም እናንተ ለሀሰተኛዉ እየሱስ ነዉ በር የምትጠርጉት እኔሰ እናንተን የማላይበት የት ልሂድ ዩቱብ በከፈትኩ ቁጥር እንዳለ ሀሰተኛ የመናፍቃን ትምህርት ነዉ የሞላዉ ኸረ ምን ይሻላል