አንደኛ መጽሐፈ መቃብያን ከምዕራፍ 1 እስከ ምዕራፍ 5
HTML-код
- Опубликовано: 10 фев 2025
- ✝️ መጽሐፈ መቃብያን ቀዳማዊ ክፍል 1 ✝️
✝️ምዕራፍ ፩፡-
-ጺሩጻይዳን ክፋትን የሚወድ፣ በፈረሶቹ ብዛትና ከሥልጣኑ በታች ባሉ በጭፍራዎች ይመካ እንደነበረና የሚያመልካቸው ብዙ ጣዖታት እንደነበሩት
-ጺሩጻይዳን በልቡናው ድንቁርና ጣዖታት ኃይልንና ብርታትን የሚሰጡት ይመስለው እንደነበር መገለጹ
-ጣዖታቱን የሚያገለግሉ ካህናት መሥዋዕቱን እነርሱ እየበሉ ጣዖቶቹ የሚበሉ አስመስለው ይነግሩት እንደነበር መገለጹ
-ጺሩጻይዳን ጣዖታቱ የፈጠሩት፣ ጣዖታቱም የሚመግቡትና የሚያነግሡት ይመስለው እንደ ነበር መገለጹ
-ጣዖታትን ሙታን ሊሏቸው እንደሚገባ መገለጹ
-ጺሩጻይዳን ትዕቢተኛ እንደነበር፣ በወንዶች አምሳል የተሠሩ ሃምሳ እና በሴቶች አምሳል የተሠሩ ሃያ ጣዖቶች እንደነበሩት መገለጹ
-ጺሩጻይዳን ጣዖታቱን የማያመልኩ ሰዎች እንዲቀጡ አዋጅ ማወጁ
✝️ምዕራፍ ፪፡-
-መቃቢስ ከነገደ ብንያም የተወለደ እንደሆነና መልከ መልካም ልጆች እንደነበሩት መገለጹ
-የመቃቢስ ልጆች እግዚአብሔርን የሚያመልኩ ስለነበሩ ለጺሩጻይዳን ጣዖታት አንሰግድም ማለታቸው
✝️ምዕራፍ ፫፡-
-እግዚአብሔር የመቃቢስን ልጆች ሰማዕትነትን እንዲቀበሉ መንገሩ
-ከመቃቢስ ልጆች ሦስቱ አብያ፣ ሲላ፣ ፈንቶስ እንደሚባሉ መነገሩ
-የመቃቢስ ልጆች ጣዖታትን አናመልክም በማለታቸው በጺሩጻይዳን የተለያዩ መከራዎች እንደደረሱባቸው
-የመቃቢስ ልጆች መከራችን ሲበዛ ዋጋችን ይበዛል ማለታቸው
✝️ምዕራፍ ፬፡-
-ጺሩጻይዳን የመቃቢስን ልጆች በድን እንዲቃጠል ማዘዙ
-እሳት የመቃቢስን ልጆች በድን ማቃጠል እንዳልቻለ ባሕርም ማስጠም እንዳልቻለ
-በጺሩጻይዳን ግዛት የሚኖሩ ሰዎች ወንዶች ልጆቻቸውንና ሴቶች ልጆቻቸውን ለአጋንንት ይሠዉ እንደነበር መገለጹ
✝️ምዕራፍ ፭፡-
-ጺሩጻይዳን በወባ ትንኝ አማካኝነት እንደሞተ
-እግዚአብሔር በተለያዩ ዘመናት ያደረጋቸው መልካም ነገሮች በጥቂቱ መጠቀሳቸው
✝️✝️✝️የዕለቱ ጥያቄዎች✝️✝️✝️
፩. ከሚከተሉት ውስጥ ስለጺሩጻይዳን ትክክል የሆነው የቱ ነው?
ሀ. በፈረሶቹ ብዛትና በጭፍራዎቹ ጽናት ይመካ ነበር
ለ. በመዓልትና በሌሊት መሥዋዕት የሚሠዋላቸው ብዙ ጣዖታት ነበሩት
ሐ. ጣዖታቱ ኃይልንና ብርታትን የሚሰጡት ይመስለው ነበር
መ. ሁሉም
፪. ስለጺሩጻይዳን የጣዖታት ካህናት ትክክል ያልሆነው የቱ ነው?
ሀ. መሥዋዕቱን ራሳቸው እየበሉ ጣዖታቱ እንደሚበሉ እየተናገሩ ይዋሹ ነበር
ለ. ሌሎች ሰዎችም ለጣዖታቱ መሥዋዕትን እንዲሠዉ ያበረታቱ ነበር
ሐ. ሰማይንና ምድርን በፈጠረ በትክክለኛው አምላክ ያምኑ ነበር
መ. ሀ እና ለ
፫. ስለመቃቢስ ልጆች ትክክል የሆነው የቱ ነው?
ሀ. መልከ መልካሞችና እጅግ ብርቱዎች እንዲሁም ደጋጎች ነበሩ
ለ. እግዚአብሔርን ያመልኩ ስለነበር ሞትን አይፈሩትም ነበር
ሐ. ለጺሩጻዳይን ጣዖታት አንሰግድም ብለው ሰማዕትነትን ተቀብለዋል
መ. ሁሉም
፬. ስለመቃቢስ ልጆች በድን ትክክል የሆነው የቱ ነው?
ሀ. ጺሩጻይዳን በድናቸውን በእሳት ሲያቃጥለው ወደ አመድነት ተለውጠዋል
ለ. በድናቸውን ወደ ባሕር ሲጥለው ሰጥሞ ቀርቷል
ሐ. በድናቸውን ባሕር ማስጠም አልቻለችም እሳትም ማቃጠል አልቻለችም
መ. ሀ እና ለ
፭. ጺሩጻይዳን የሞተው በምንድን ነው?
ሀ. ጦር ሜዳ ሄዶ በጦር ተወግቶ
ለ. የወባ ትንኝ ነክሳው በወባ ትንኝ ምክንያት
ሐ. ጠላቶቹ መርዝ አጠጥተው ወደ ገደል ጥለውት
መ. መልስ የለም
አሜን አሜን አሜን ቃል ህይወት ያሰማልን የአገልግሎት ዘመናቸውን ይባርክልን አበታችን አሜን አሜን አሜን 🙏❤️❤️