አንደኛ መቃብያን ከምዕራፍ 6 እስከ ምዕራፍ 10
HTML-код
- Опубликовано: 10 фев 2025
- 💞 መጽሐፈ መቃብያን ቀዳማዊ ክፍል 2 💞
💞ምዕረፍ ፮፡-
-እግዚአብሔር ፈቃዱን የሚያደርጉ ነገሥታቱን እንደሚያነግሥ
-የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርጉ ነገሥታት በመንግሥተ ሰማያት እንደሚኖሩ
-ደጋግ ነገሥታት በዚህ ዓለም ሳሉ በጎ ሥራን እንደሚሠሩ መገለጹ
-ክፉ ነገሥታት የድኾችን ጩኸት ቸል እንደሚሉና የተገፋውን ሰው እንደማያድኑ
💞ምዕራፍ ፯፡-
-ንጉሥ እግዚአብሔር እንደሾመው በሚገባና በእውነት መፍረድ እንደሚገባው
-ንጉሥ የእግዚአብሔርን ቃል መስማትና ትእዛዙንም ማድረግ እንደሚገባው
-ምድራዊ መንግሥት ኃላፊ እንደሆነ መገለጡ
💞ምዕራፍ ፰፡-
-ትንሣኤ ሙታን በተክልና በአዝርዕት ፍሬ፣ በሰው መተኛትና መንቃት፣ በፀሐይ መግባትና መውጣት መመሰሉ
-በትንሣኤ ለሁሉም እንደሥራው እንደሚከፈለው ማሰብ እንደሚገባና መስነፍ እንደማይገባ
-የእግዚአብሔር የሕይወት ጠል ካልወረደ ሙታን እንደማይነሡ መገለጹ
💞ምዕራፍ ፱፡-
-በዕለተ ትንሣኤ ተራሮችና ኮረብቶች፣ ወንዞችና ጥልቆች እንደ ጥርጊያ ጎዳና እንደሚሆኑና ሥጋ ለባሽም ሁሉ ትንሣኤን እንደሚነሣ መገለጹ
💞ምዕራፍ ፲፡-
-እግዚአብሔር ሰውን ካለመኖር ወደ መኖር እንዳመጣው ሁሉ የሞተውን ሰውም እንደገና እንደሚያስነሣው መገለጡ
💞💞💞የዕለቱ ጥያቄዎች💞💞💞
፩. ስለደጋግ ነገሥታት ትክክል ያልሆነው የቱ ነው?
ሀ. የድኻውን ጩኸት ቸል ይላሉ
ለ. የእግዚአብሔርን ፈቃድ ይፈጽማሉ
ሐ. ከሞት በኋላ በመንግሥተ ሰማያት ይኖራሉ
መ. በዚህ ዓለም ሳሉ በጎ ሥራን ይሠራሉ
፪. ስለ ክፉ ነገሥታት ትክክል የሆነው የቱ ነው?
ሀ. ከሞት በኋላ ወደ ሲኦል ይወስዷቸዋል
ለ. በእውነትና በሚገባ አይፈርዱም
ሐ. የተራቡትን አይመግቡም የተጠሙትንም አያጠጡም
መ. ሁሉም
፫. በመጽሐፈ መቃብያን መሠረት ከሚከተሉት ውስጥ ለትንሣኤ ሙታን ምሳሌ የሆነው የቱ ነው?
ሀ. የፀሐይ መግባትና መውጣት
ለ. የአዝርዕትና የአትክልት ፍሬ መፍረስና መብቀል
ሐ. የሰው መተኛትና መንቃት
መ. ሁሉም
፬. ስለ መጨረሻው ትንሣኤ ሙታን ትክክል የሆነው የቱ ነው?
ሀ. እንሳስትና አራዊት ከሙታን ይነሣሉ
ለ. አዕዋፋት ከሙታን መካከል ይነሣሉ
ሐ. ሰው የሆነ ሁሉ ከሙታን ይነሣል
መ. ከሰው መካከል ኃጥኣን ሞተው ይቀራሉ እንጂ በትንሣኤ ጊዜ አይነሡም