የህይወት ውሃ -ቢንያም አየለ | Ye hiwot weha -BINIYAM AYELE |NewEthiopianGospel Music
HTML-код
- Опубликовано: 16 сен 2024
- ዮሐንስ 7 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³⁷ የበዓሉ መጨረሻ በሆነው በታላቁ ቀን፣ ኢየሱስ ቆሞ ከፍ ባለ ድምፅ እንዲህ አለ፤ “ማንም የተጠማ ቢኖር ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣ፤
³⁸ በእኔ የሚያምን፣ መጽሐፍ እንዳለ የሕይወት ውሃ ምንጭ ከውስጡ ይፈልቃል።”
³⁹ ይህን ያለው በእርሱ የሚያምኑ ስለሚቀ በሉት መንፈስ ነበር፤ ምክንያቱም ኢየሱስ ገና ስላልከበረ መንፈስ አልተሰጠም ነበር።
ዮሐንስ 4 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁸ ደቀ መዛሙርቱ ምግብ ለመግዛት ወደ ከተማ ሄደው ነበር።
…
¹³ ኢየሱስም እንዲህ ሲል መለሰላት፤ “ከዚህ ውሃ የሚጠጣ እንደ ገና ይጠማል፤
¹⁴ እኔ ከምሰጠው ውሃ የሚጠጣ ግን ከቶ አይጠማም፤ እኔ የምሰጠው ውሃ በውስጡ የሚፈልቅ የዘላለም ሕይወት ውሃ ምንጭ ይሆናል።”
¹⁵ ሴትዮዋም፣ “ጌታዬ፤ እንዳልጠማና ውሃ ለመቅዳት እንዳልመላለስ፣ እባክህ ይህን ውሃ ስጠኝ” አለችው።
መዝሙር 23 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ እግዚአብሔር እረኛዬ ነው፤ አንዳች አይጐድልብኝም።
² በለመለመ መስክ ያሳርፈኛል፤ በዕረፍት ውሃ ዘንድ ይመራኛል፤
³ ነፍሴንም ይመልሳታል። ስለ ስሙም፣ በጽድቅ መንገድ ይመራኛል።