የማቴዎስ ወንጌል ትምህርት 10-ብፁዓን ናቸው(ክፍል 1) በማሙሻ ፈንታ-Matthew Teaching 10-Blessed Are...(Part 1) By Mamusha F
HTML-код
- Опубликовано: 11 окт 2024
- ይህ ትምህርት በኢትዮጵያ የሕይወት ብርሃን ቤተ ክርስቲያን፣ በአዲስ ክርስቲያን ላይፍ አሴምብሊይ አጥቢያ ዘወትር አርብ በማሙሻ ፈንታ እየተዘጋጀ የሚቀርብ ነው።
ትምህርቱን በቀጥታ ስርጭት መከታተል ለምትፈልጉ
ዓርብ ምሽት 11:30 - 1:30
Yoututube - Equip Media / @equipmedia2577
Facebook - Equip Media Mamusha Fenta
/ 312726798871156
አድራሻችን፡ ካዛንቺስ ከመለስ ዜናዊ ፋውንዴሽን ባሻገር 200 ሜትር ገባ ብሎ
ጉግል ማፕስ - google maps address
maps.app.goo.g...
#እነሆ_ንጉሥሽ
#የማቴዎስ_ወንጌል_ትምህርት_10
#ብፁዓን_ናቸው (ክፍል 1)
#በማሙሻ_ፈንታ
📖 ማቴ 5:1-12
- "የተራራው ስብከት" የሚባሉት ከማቴ 5 - 7 ያሉት ክፍሎች ናቸው።
- በማቴዎስ ወንጌል 5 የተለያዩ ክፍሎች አሉ፤ የመጀመሪያው ይሔ ነው።
- የተራራው ስብከት መነሻው ምዕራፍ 4:23-25 ላይ ነው፤ የኢየሱስ አገልግሎት እጣሬ ነው።
* እያስተማረ
* እየሰበከ
* እየፈወሰ ይዞር ነበር። በዚህ ምክንያት ዝናውም ወጣ፤ ህዝቡም ወደሱ ይጎርፍ ጀመረ። ኢየሱስስ ምን አደረገ? ምዕ 5: 1 ወደ ተራራ ዞር አለ።
- የኢየሱስ ዋና አገልግሎት ማስተማር ነበር። ሁሉ ነገር ወደማስተማር ካልመጣ ኪሳራ ነው። ኢየሱስ ተአምራት ያደርጋል፤ አጋንንት ያወጣል፣ ይፈውሳል ግን ይሔ ሁሉ ወደ ትምህርት ለማምጣት ነው።
- ኢየሱስ ዝም ብሎ ተአምራትን እያደረገ የሚኖር አልነበረም፤ ይሰብክም ነበር።
- እነማንን ነው የተራራውን ስብከት ያስተማራቸው? ቁ.1-2
* ደቀመዛሙርትንም (ተከታዮቹንም፤ ተማሪዎቹንም)
* ሕዝቡንም
📖 ማቴ 7:28 ..ሕዝቡ በትምህርቱ ተገረሙ
- በተራራው ላይ ያስተማረው የመጀመሪያው ሕግጋቱን ነው (ከምዕ 5-7)
- ኢየሱስ ሕግ ፈጻሚ እንጂ አፍራሽ አይደለም። የሕቱ ትርጓሜን ይሰጣል እንጂ አይጥልም።
📖 ማቴ 5:17
* እግዚአብሔር የምግባር ሕግጋቱን አልቀየረም የምንፈጽምበትን ጉልበት ሰጠን እንጂ።
📖 ማቴ 7:14
- የብሉይ ኪዳን ሕግጋት በአዲስ ኪዳን መተርጎም፤ መተንተን፤ መብራራት ስላለባቸው ለሱ ነው የመጣው።
- የተራራው ስብከት ክፍሎች (5-7)
1) ከቁ 3-16 - መግቢያ
2) ከ5:17 - 7:12- ዋናው ትምህርት
3) 7:13 - 27 - ማጠቃለያ
🛑 መግቢያ
* ኢየሱስ ያስተማራቸው ብፅናዎች (3-12)
- ብፁዓእን :- የተባረኩ፣ ደስተኞች፣ እግዚአብሔር የተቀበላቸው፣ በእግዚአብሔር ዘንድ የተወደደ ሕይወት ያላቸው፣ የእግዚአብሔርን ሞገስ ያገኙ ናቸው።
- ለመግባት የሰሩት ሳይሆን ስለተቀበላቸው የሆኑት ባህሪያት ናቸው። እግዚአብሔር መንግስት የገቡ ግን እነዚህን የመሠሉ ባህርያት አላቸው።
- የእግዚአብሔር መንግስት ወደፊት የምንጠባበቃት ብቻ ሳትሆን አሁን የምንገባባት ናት።
- ብፅዕና ሰርተን የምናገኛቸው ሳይሆኑ ወደ እግዚአብሔር ስለገባን ያገኘናቸው ናቸው።
- ብፅዕና ለጥቂት ሰዎች ብቻ የተሰጠ አይደለም። በክርስቶስ በኩል ወደ እግዚአብሔር እንምጣ፤ ክርስቶስን እንቀበል እንጂ ሁላችን ብፁዓን ነን።
- እግዚአብሔር ወደመንግስቱ በኑሮ ምዘና አላስገባንም፤ የገቡ ግን ኑሯቸው ሲመዘን እነዚህ ባህርያት ይገኙባቸዋል።
- የእግዚአብሔር መንግስት በአድርግ አታድርግ አይገባባትም።
- ክርስትና ሲፈተሽ ህይወት አለው፤ ባህርይ አለው። ተደርጎልሀል፤ ሆኖልሀል ብቻ አይደለም የሕይወት ኳሊቲ ይጠይቃል።
- እግዚአብሔር የተቀበላቸው ባህርያት ምንድናቸው?
1) በመንፈስ ድሆች የሆኑ
2) የሚያዝኑ
3) ጽድቅን የሚራቡና የሚጠሙ
- የእግዚአብሔር ሕዝብ ቀጥታ ከእግዚአብሔር ጋር ያላቸውን ግንኙነት የሚያሳዩ ናቸው።
- የመንግሥቱ ሕዝብ መታወቂያዎች ናቸው።
1) የመንፈስ ድህነት ምንድነው ?
- ከባዶነት የጀመረ ህይወት ያላቸው፤ በተሰበረ ልብ ህይወታቸው የጀመረ ናቸው።
- ሰው ቁሳዊ ሀብትና ንብረት ኖሮትም በመንፈስ ድሀ ሊሆን ይችላል። (ማቴ 19)
- ሰው ገንዘብ ፣ ሀብት ንብረት የማይሞላው ማንነት አለው።
- በመንፈስ ድሆች የተሰበረ ልብ ያላቸው፣ ትምክህት የሌላቸው፣ በትህትና ዝቅ ያሉ፣ የተዋረደ መንፈስ ያላቸው፣ በእግዚአብሔር ፊት በትህትና የሚገቡ፣ አልችልም የሚሉ፣ በራሳቸው የማይቆሙ ናቸው።
📖 ሉቃ 48:9-14
- እግዚአብሔር ሊሞላን ሲፈልግ መጀመሪያ ትጥቅ ያስፈታናል።
- የእግዚአብሔር መንግሥት የትምክህት አይደለችም፤ መሞላት የሚፈልጉ ከባዶነት ነው የሚጀምሩት።
- የጸደቀ ሰው ጽድቅን አይጠግብም።
- ለእግዚአብሔር መሠበር ጥሩ ነው። ከእግዚአብሔር ጋር ባለ ግንኙነት ካልተሰበርን አንጠገንም።
- የተባረከ ህይወት በትምክህት አይገኝም፤ በእግዚአብሔር ፊት በትህትና በመሆን እንጂ።
2) የሚያዝኑ
- ሀዘን ቁጭ ብለው ሲቆዝሙ ይውላሉ ማለት አይደለም።
- ክርስትና አለመሳቅ አይደለም፤ ደስታ ነው።
- በራሳቸው ድካም፣ በዙሪያቸው በሚያዮአቸውም ድካም፣ በሀጢአት፣ ስላልዳኑ ሰዎች፣ ያዝናሉ ።
3) የጽድቅ ረሀብና ጥማት
- ጽድቅ፦ ከእግዚአብሔር ጋር ያለ ትክክለኛ ኑሮ ማለት ነው።
- እግዚአብሔር የሚከብርበት ነገር በተመለከተ ሁልጊዜ ረሀብተኛ ናቸው።
- ሁልጊዜ ይጠማሉ አንድ ነገር ላይ አይቆሙም፤ ይበቃኛል አይሉም።
- እውነተኛ የእግዚአብሔርን ነገር መለማመዳችንን የምናውቀው ሁልጊዜ ቀጣዩን እንጠማለን።
ትህትና ይብዛልን
Amen tihwuti nafisi egzaberini yayutali❤@@selamugenetu9253
ክቡር ሁሉ ለልኡል እግዚአብሔር አምላክ ይሁን.. ዶ/ር ማሙሻ እና ዶ/ር አብርሃም እና ሌሎች በዚህ አግልግሎት እያነጻቹን ያላቹ እግዚአብሔር አምላክ አብዝቶ ይባርካቹ ሁላቹሁም ተባረኩልኝ 🙏🏽🔥🔥🔥
ተባረክልኝ ዶ/ር
እግዚአብሔር ይባርካችሁ መላው የዚህች ቤተክርስቲያን አገልጋዮች ።
አሜን ያልገባኝን የማላውቀውን ጌታ በእናንተ አልፎ እያሳወቀኝ .........
ጌታ የሱስ አብዝቶ ይባርካችሁ ፡፡
ዶ/ር ማሙሻ ተባረክ ለበረከት ሁን
እግዚአብሄር ይባርክህ 👏👏🙏🙏🙏🙏
እሜን! የሚያዝን: የተጠማ; የተሰበረ ልብ አብዛልን ጌታ ሆይ!!!! ተባረክ ዶክተር ማሙሻ ታንክዩ ❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤
የሚገርም የህይወት መመሪያ ነዉ። ተባርካሀል ዶክተር ማሙሻ።
ጌታ ኢየሱስ አብዝቶ ይባርካችሁ 👏👏🙏
ዶክተር ማሙሻ ሌሎች ወንድሞችም ጌታ ኢየሱስ ይባርካችሁ ጸጋውን ያብዛላችሁ ።
ጌታ የሱስ ክርስቶስ ይባርካችሁ እኔ ይህን ቭደው እየተከታተልኩ ብዙ ተጠቃም ሆኛለሁ ጌታ በመንፈሱ ከእናንተ ጋር ይሁን፡፡
Amennnnn ዘመናቹ ይለምልም የቃሉ ፍቺ ያበራል አላዋቂን ጠቢባን ያደርጋል ጌታ ልቤን ያብራ
አሜን ጌታ ሆይ
Egziabiher Amlak ybarkh Doctor mamush.
እግዚአብሄር ብርክ ያርጋቹ የተማርነው የምንኖር ያርግልን
Thank you Jesus for brothers who feed
us your precious word.
Amen amen 🙏 bless you mamush ,👍🙏♥️
ብፅዕና
Amenn.Amennn.aba ameseginhalehu🙏🙏🙏 dr mamusha tebarek
ወንድሜ ማሙሻ በዕውነት በትምህርትህ ሁሌ ነው የምባረከውም የምታነጸውም እንዳስብም ራሴንም እንዳሰላስለው ያደርገኛል በዚህ ነገር ሁሉ ጌታ አብዝቶ ይባርክህ
ተባረኩ
geta yibarkrk
ማሙሻ ኑርልን 👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏
AMEN AMEN GETA HOY ERDAN🙏🙏🙏🙏
God bless you more and more
Thankyou D/r you is Righteous really the kingdom preachers!!!
Good bless you Dr Mamusha ur our blessing
Stay blessed our dear brother!
ዘመንህ ይባረክ!!!
ዘመናችሁ ይባረክ በዚህ አገልግሎት የተሳተፋችሁ ሁሉ በጣም እየተጠቀምኩ ነዉ ጌታ ይባርካችሁ;:☺😊
ተባረክ ዶ/ር ማሙሻ ጌታ ይባርካችሁ፡፡
አሜን🙏🏾
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
Dr Mamusha I missed you God bless you
ዶ/ር ማሙሻ እግዚያብሔር ይባርክህ። አብረውክም ተጠምደው የእግዚአብሔርን ስራ የሚሠሩ ሁሉ ይባረኩ።
ትውልዳችሁ፡ያተበራካ፡ይሁን።
Amen Pastor ስትሄዱ እንዳትረሱኝ። በጣም ጥሩ ሃሳብ ነው ። እግዚአብሔር ይረዳናል።
ጌታ ይባርካችሁ አገልግሎታችሁ ይባርክ። እባካችሁ ጊታሩ ለይ ያለው ባንዲራ ያለ ማሰተዎል ይመስለኛል የዘመኑን ሬንቦ ይመስላልነ አንሱት ጠላት በብዙ እየሰራ ያለበት ዘመን ስለሆነ እነስተውል ባንዲራውን ሌላ ቦታ ብታደርጉት መልካም ነው። ተባረኩ
Geta yimesgen
የምወደው ከስወች ጋር ያለኝ ግንኙነት ትክክል ሳይመስለኝ ሲቀርና ዝለት ሲመጣብኝ ሮጨ የማነበው ማቴዎስ 5-7 ይህን ክፍል ከጀመርኩ መውጣት ይቸግረኛል ምክኒያቱም ራሴን በዛ ውስጥ አየዋለሁና ።
የኢትዮጵያ ወጣቶች ይህም አይነት ኢትዮጵያውያን እንዳሉ እወቁ ኩሩ ተከተሉ ተስተካከሉ። እኛ የምናእቃት ኢትዮጵያ ፣ በየአለሙ የምንሰፈሰፍላት ኢትዮጵያ ይህች ናትና፣ ጠብቁአት አክብሩአት፣ ዞሮ መግቢያችን ኢትዮጵያ ይህች ናት።
ጊታሩ ላይ ያለው አርማ ሌላ ነገር ይመስላል እባካቹ ነገር ለሚቆረቁሩ ጥሩ መስሎ አልታየኝም የጌዎች ባንዲራ ሊመስል ይሄዳል ፕሊስ ቅዱሳን ጥንቃቄ
እኔም መስሎኛል 😮😮
በምድረ በዳ ሆኖ ጌታን መጠማት ምንም በሌለበት ተስፋ በሚያስቆርጥ ስፍራ የውሀ ጥም በሚያንገላታበት ስፍራ እግዚአብሔርን መንፈስ መጠማት የመንፈስ ድሀ መሆን ጌታ ይጨምርልኝ ተባረክ ዶር ማሙሻ የሚያስተምር መንፈስ ቅዱስ ስሙ ብሩክ ይሁን
Amen amen
ትህትና የልብ ሀሳብ /motive /ነው እንጂ መቅለስለስ አይደለም ጮክ ብሎ በድፍረት መናገር ትህትና አይደለም ልንል አንችልም በተለይ እኛ ሀገር የትህትና ትርጉም የተሳሳተ ነው። እ/ር ናችሁ ያለንን ነን ማለት ትእቢት አይደም