ፆም ምንድ ነው ? ቻናሉን

Поделиться
HTML-код
  • Опубликовано: 16 окт 2024
  • #ጾምምንድንነው? ለምንስ እንጾማለን?
    ጾም በፊደላዊ ትርጉሙ “ጾመ” - #ተወ ፥ #ታቀበ ፣#ታረመ ካለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ቃል ነው፡፡ የቃሉ ፍች ምግብ መተው መከልከል ፣መጠበቅ ማለት ነው፡፡ በዕብራይስጥና በሱርስት ቋንቋዎች “ጾም” ሲባል በዐረብኛ ደግሞ “ጾመ” በመባል ይጠራል፡፡ ስለዚህ ጾም ለክፉ ሥራ ከሚያነሣሱ የምግብ ዓይነቶች ፤በቤተ ክርስቲያን የሥርዓት መጸሕፍት ከተወሰነው ጊዜ ሳያጓድሉ መከልከል ወይም ለተወሰነ ጊዜና ሰዓት ሰውነት ከሚፈልጋቸው ነገሮች ሁሉ መወሰን (መታቀብ) ማለት ነው፡፡ ለሰውነት የሚያምረውንና የሚያሰጎመዠውን ነገር ሁሉ ስለ ፍቅረ እግዚአብሔር ብሎ መተውም ነው
    ጾመ ማለት ደግሞ ጥሉላት መባልዕትን ፈጽሞ መተው፣ ሰውነትን ከመብልና ከመጠጥ ከሌላውም ክፉ ነገር ሁሉ መጠበቅ፣ መግዛት፣ መቆጣጠር፣ በንሰሓ ታጥቦ በጸሎት ወደ እግዚአብሔር መቅረብና እርሱንም ደጅ መጥናት፣ ማረኝ ፣ይቅር በለኝ በማለት በቅድመ እግዚአብሔር በመንበርከክ ምሕረተ አምላክን ለመቀበል መዘጋጀት ነው፡፡ የቤተክርስቲያናችን የሥርዓትና የሕግ መጽሐፍ ፍትሐ ነገሥት በአሥራ አምስተኛው አንቀጽ ጾምን እንዲህ ይተረጉመዋል፡- “ጾምስ ተከልኦተ ብእሲ እመብልዕ በጊዜ እውቅ በውስተ ሕግ-ጾምስ በታወቀው ዕለት በታወቀው ሰዓት ሰው ከምግብ የሚከለከለው መከልከል ነው፡፡” አንድም ከሊዓ ብእሲ ይላል ጾም ሰውን ከምግብ መከልከል” ነው፡፡ ይህም ዋጋውን ለማብዛት እርሱ ወዶ ሕግን ለሠራለት እየታዘዘ የፈቲውን ኃይል ያደክም ዘንድ ሥጋም ለነባቢት ነፍስ ትታዘዝ ዘንድ ነው፡፡
    ጾም ከመንፈሳዊ ተጋድሎዎች አንዱ ነው፡፡ ለሥጋም መንፈሳዊ ልጓም ነው፡፡ ጸዋሚ ሰው ፈቃደ ሥጋውን እየገታ ነፍሱን የሚያለመልምበት ስንቅ ነው፡፡ “ጾም ቁስለ ነፍስን የምትፈውስ፣ ኃይለ ፍትወትን የምታደክም የበጎ ምግባራት ሁሉ መጀመሪያ፣ ከእግዚአብሔር ጸጋን የምታሰጥ፣የወንጌል ሥራ መጀመሪያ፣የጽሙዳን ክብራቸው፣የድንግልና የንጽሕና ጌጣቸው፣የንጽሕና መገለጫ፣ የጸሎት ምክንያት እናት፣የዕንባ መገኛ መፍለቂያዋ፣ አርምሞን የምታስተምር፣ ለበጎ ሥራ ሁሉ የምታነቃቃ፣ ሰውነትን በእግዚአብሔር ፊት በማዋረድ ትሕትናን ገንዘብ ለማድረግ የምትረዳ መድኃኒተ ነፍስ ናት፡፡” ማር ይስሐቅ አንቀጽ ፬ ምዕ.፮
    “ጾም ተድላ ሥጋን የምታጠፋ፤ የሥጋን ጾር የምታደክም ፤ቁስለ ነፍስን የምታደርቅ፤ ለጎልማሶች ጸጥታንና ዕርጋታን የምታስተምር፤ ከግብረ እንሰሳዊ የምትከለክል፤ ሰው መላእክትን መስሎ የሚኖርባትና ኃይል መንፈሳዊን የሚጎናጸፍባት ደገኛ መሣሪያ ናት፡፡“ /ፆመ ድጓ/
    ከኃጢአት ፆር ከፍትወት አንዱንምአንዱን ድል መንሳት ለማጥፋት፥ የዲያብሎስን ረቂቅ ፍላጻ ለመመከት በጾም መድከም የሥራ ሁሉ መጀመሪያ እንደሆነች የታወቀ ነው፡፡ ጾም የምሕረት መለመኛ፤ የንሰሐ መገለጫ፤ ከመከራ የሚሠወሩባት፤ሰውንከእግዚአብሔር ጋር አስታርቃ ርስት መንግሥተ ሰማያት የሚታስገባ “ኆኀተ ጽድቅ - የጽድቅ በር” ሆና የተሰጠች ቀዳማዊ ሕግ ናት፡
    “ዠጾም ሰውን ከእግዚአብሔር ጋር አስታርቃ ርስት መንግሥተ ሰማያት የምታስገባ “ኆኅተ ጽድቅ የጽቅ በር” ሆና የጠሰጠች ቀዳማዊ ሕግ ናት” /ኩፋሌ. ፬÷፰፣ ዘፍ. ፪÷፲፮/
    “በፍጥረት መጀመሪያ ሰውን ከዓለም እንስሳት ከለዩት ነገሮች አንዷ የበጎ ነገር መገኛ መከማቻ የምትሆን ጾም ነበረች” /ዘፍ. ፫÷፲-፳፬/
    ጾም ልንጠቀምበት ከአግዚአብሔር የተሰጠን ስጦታ ጸጋና በረከትም ነው፡፡ እንጂ የታዘዝነው ሕግ ብቻ አይደለም” /ማቴ. ፭÷፮/ “ሃይማኖት ባለበት ሁሉ ጾም አለ፣ የክርስቲያኖች ሕይወት ከጾም ተለይቶ አይታሰብም”
    ጾም ለምን ይጠቅማል?
    ፩. ፈቃደ ሥጋን ለፈቃደ ነፍስ ለማስገዛት ይጠቅማል፡፡
    “ጾም ትፌውስ ቁስለ ነፍስ ወታደምም ኵሎ ፍትወታተ ዘሥጋ (ጾም የነፍስን ቁስል ታደርቃለች ተድላ ሥጋን ታጠፋለች” /ቅዱስ ያሬድ/
    ፪. ጾም ንስሐ ለመግባት ይጠቅማል፡፡
    “ጾም ወደ እግዚአብሔር ለመመለስ፤ ልብን ለማቅናት ለመጸጸትና ንስሐ ለመግባት ይጠቅማል፤ (----በፍጹም ልባችሁ በጾምም በልቅሶም በዋይታ ወደ እኔ ተመለሱ)” ትንቢተ ኢዮ. ፪÷፲፪፡፡ በጾምና ጸሎት ወደ እግዚአብሔር የተመለሱ ድኅነትን እንዳገኙ ሁሉ በንስሐ ያልተመለሱ ደግሞ ጠፍተዋል ለምሳሌ፡-
    • የዳኑ፡- ሰብዐ ነነዌ (የነነዌ ሰዎች)
    • የተቀጡ፡- ሰብዐ ሰዶም ገሞራ (የሰዶምና የገሞራ ሰዎች) ዘፍ. ፲፱÷፳፫
    ሰብዐ ትካት (በኖኅ ዘመን የጠፉ የመከራ ሰዎች) ዘፍ. ፯÷፲፫
    ፈርዖንና ሕዝቡ ዘጸ. ፯÷፳፣ ፲፬÷፳፰
    • የተወቀሱ፡- ኮራዚን፣ ቤተ ሳይዳ፣ ቅፍርናሆም ማቴ ፲፩÷፳
    ፫. ጾም ኃይለ አጋንንትን ለማድከም ጸብእ አጋንንትን ለማብረድና ለማስወገድ ይጠቅማል፡፡ “ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከተጠመቀ በኋላ ሳይውል ሳያድር ወደ ገዳመ ቆሮንጦስ ሄደ፤ በዚያም አርባ መዓልትና አርባ ሌሊት ጾመ፣ ጸለየ በዚያም ኃይለ አጋንንትን ጸብእ አጋንንትን ድል ነስቷል፡፡” ማቴ ፬÷፩ ጌታችን በዚህ ጾም ሦስቱን አርእስተ ኃጣውእ (የኃጢአት ራሶችን) ድል ነስቷል፡፡
    • ስስት፡- ያልሰጡትን መፈለግ በተለይ የመነኮሳት ጾር ነው፡፡ ጌታችን በትዕግሥት ድል አድርጓል፡፡
    • ትዕቢት፡- ሥልጣናትን ረቂቅ ዕውቀታችን ምጡቅ በማለት የካህናት ጾር ነው፡፡ ጌታችን በትሕትና ድል አድርጓል፡፡
    • ፍቅረ ንዋይ፡- በቃኝ አለማለት የነገሥታት ጾር ነው፡፡ በጸሊአ ነዋይ (ንዋይን በመጥላት) ድል አድርጓል፡፡
    “ዝንቱ ዘመድ ኢይወጽእ ዘእንበለ በጾም ወበጸሎት” - ይህ ዓይነቱ አብሮ አደግ ጋኔን በጾምና በጸሎት ካልሆነ በቀር አይወጣም ማር. ፱÷፲፬፣ ማቴ. ፲፯÷፳፩፡፡
    ፬. ከእግዚአብሔር መልካም ነገርን እንድንቀበል ይረዳናል (ይጠቅመናል)
    • ሰው ከእግዚአብሔር ጸጋና በረከትን ይቅርታና ምሕረትን ለማግኘት ይጾማል፡፡
    • ጾም የበጎ ነገር መከማቻ የጸሎትም እናቷ ናት፡፡
    በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የብዙ አባቶችን ሕይወት ብንመለከት በጾ በጸሎት በበረከት መልካም ነገርን በመቀበል የተሞላ ነው፡፡ ለምሳሌ፡-
    ሊቀ ነቢያት ሙሴ፡- (ዘጸ. ፴፬÷፳፰-፴፩ ዘዳ. ፱÷፱፡፡
    o ሕገ ኦሪትን ታቦተ ጽዮን ተቀብሏል፡፡
    o ገጹ እንደ ፀሐይ ያበራ ነበር፡፡
    o ሠልስቱ ደቂቅና ነቢዩ ዳንኤል፡- ትን. ዳን. ፩÷፰፡፡
    o ፊታቸው አዕምሮና ሥጋቸው ወፍሮ ታየ፡፡
    o ዕውቀትና ማስተዋል ተሰጥቷቸዋል፡፡
    ቅዱሳን ሐዋርያት፡- ሐዋርያት በጾም የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ ተቀብለዋል ሐዋ. ሥ. ፲፫÷፩፣ ፩ኛ ቆሮ. ፲፩÷፳፯-፳፰
    ፭. ጾም በምርኮ ላይ ስላሉ ወገኖች፣ ስለ ሀገር ኅዘንን ለመግለጽ ይጠቅማል፡፡
    • ስለ ተሰደዱ፣ ስለታሠሩ፣ ስለ ተጨነቁ፣ በጦርነት ስለሚሰቃዩ፣ በደዌ ዳኛ በአልጋ ቁራኛ ስለተያዙ….. ወገኞች በማዘን ከእግዚብሔር ምህረትን ለመለመን ይጠቅማል፡፡
    • ጾም ስለ ራሳችንንና ከሃይማኖት፣ ከምግባር፣ ከትሩፋት ርቀው በኃጢኣት ለደከሙት ማዘን ነው፡፡ “ለደካሞች ትጉላቸው” ፩ኛ ተሰ. ፭÷፲
    • መከራ መስቀሉን፣ ሞተ ወልደ እግዚአብሔርን፣ ግፉ ሰማዕታትን ለማሰብ ጾም ጸሎት ይጠቅማል፡፡
    የነህምያ ጾምና ጸሎት መ. ነህ. ፩÷፪
    የእዝራ ጾም መ. ዕዝ. ፲÷፮
    የጾም ዓይነቶች፡-
    በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስተምኅሮ መሠረት ጾም በሁለት ይከፈላል፡፡
    ፩. የዐዋጅ /የሕግ/ ጾም
    ፪. የግል ጾም
    የዐዋጅ/የሕግ ጾም
    በዐዋጅ ለሕዝቡ ተነግሮ ሕዝቡ በሁሉ ዐውቆት በአንድነት የሚጾመው ጾም የዐዋጅ ጾም ይባላል፡፡ ይህ ዓይነቱ ጾም ከንቱ ውዳሴ የሌለው ፈሪሳዊም የማያሰኝ የሕግ ጾም ነው፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ብንመለከት ይህን ዓይነቱን የዐዋጅ ጾም የጾሙ ጾሙን ያወጁ እና በጾሙ የተጠቀሙ ብዙ ሰዎችን መመልከት ይቻላል ለምሳሌ፡-
    • ካህኑ ዕዝራ ለአኃዋ ወንዝ ጾምን ዐውጆ ነበር መ. ዕዝ. ፰÷፳፩
    • ነህምያና ሕዝቡ ለአንድነት ጾመዋል ነህ ፱÷፩
    • ጾመ ኢዮሳፍጥ (ኢዮሳፍጥ) ያወጀው ጾም ፪ዜና ፳÷፩
    • የነቢዩ ኤርምያስ የአዋጅ ጾም ት. ኤር. ፴÷፱
    • ጾመ አይሁድ (ፈሪሳውያን) ሰኞና ሐሙስ ሉቃ. ፲፰÷፲፪፣ ማር. ፪÷፲፱
    • ሕዝበ እስራኤል የወሰኑት የጾም ወራት ት. ዘካ. ፰÷፱
    • የሐዋርያት ጾም (የጾም ወቅት) ሐዋ. ፳፯÷፱፣ ሐዋ. ፲፫÷፩
    በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሥርዓት መሠረት ዕድሜያቸው ከ፯ ዓመት በላይ ያሉ ለአቅመ አዳምና ሔዋን የደረሱ ሁሉ አንዲጾሟቸው የታወጁ መጀመሪያቸውና መጨረሻቸው ተቀምሮ ጊዜና ወቅት ተወስኖላቸው የተደነገጉ ሰባት የዐዋጅ አጽዋማት አሉ፡፡
    እነዚህ አጽዋማት በሐዋርያት ሲጾሙ የቆዩ በቀኖና የጸኑ በሥርዓት መጻሐፍት ሥርዓታቸው የተሠራላቸው ናቸው፡፡ የጾም መግቢያ ቅበላ ሲባል ፍጸሜው ደገሞ ፍስክ (ተፈሰከ) ተገደፈ ይባላል፡፡
    ሰባቱ የዐዋጅ አጽዋማት
    ፩. ዐቢይ ጾም (ጾመ ሁዳዴ)
    ይህ ጾም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከተጠመቀ በኋላ ፵ መዓልትና ፵ ሌሊት የጾው ጾም በመሆኑ ዐብይ ተብሏል፡፡ /ማቴ ፬/
    ፪. የሰኔ ጾም (ጾመ ሐዋርያት)
    ይህ ጾም ሐዋርያት የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ ከተቀበሉ በኋላ ለስብከተ ወንጌል ከመሠማራታቸው አስቀድሞ የጾሙት ጾም ነው፡፡ ማቴ፱÷፲፬-፲፰
    ፫. ጾመ ፍልሰታ (ጾመ ማርያም)
    ይህ ጾም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ዕረፍቷን፣ ትንሣኤዋንና ዕርገቷን የምናዘክርበት ታላቅ ጾም ነው፡፡ መዝ ፻፴፩÷፲ መኀ. ፪÷፲
    ፬. ጾ

Комментарии • 5