ሦስተኛ መቃብያን ከምዕራፍ 6 እስከ ምዕራፍ 10

Поделиться
HTML-код
  • Опубликовано: 10 фев 2025
  • 💙 ሦስተኛ መጽሐፈ መቃብያን ክፍል 2 💙
    💙ምዕራፍ ፮፡-
    -የምንሞትበትን ቀን ማሰብ እንደሚገባ
    -እግዚአብሔርን የሚፈሩ ሰዎችን አጋንንት እንደሚፈሯቸው
    -ኃጥኣን ዘመናቸው ሳያልፍ ንስሓ መግባት እንደሚገባቸው
    -ያለ ልክ የጠገበች ሰውነት እግዚአብሔርን እንደማታስብ
    -ያለ ልክ መብላትና መጠጣት ማመንዘርም እንደ እሪያ መሆን እንደሆነ
    -በልክ የሚበላ ሰው በእግዚአብሔር መሠረት እንደ አድማስ የጸና እንደሚሆን
    -እግዚአብሔርን የማይወዱ ሰዎች ቃሉን እንደማይጠብቁና ልቡናቸውም የቀና እንዳልሆነ
    💙ምዕራፍ ፯፡-
    -በእግዚአብሔር የሚያምኑ ሰዎች ፍርሃት እና ድንጋጤ እንደሌለባቸው
    💙ምዕራፍ ፰፡-
    -ኢዮብ በደረሰበት መከራ ልቡን እንዳላሳዘነ መገለጹ
    -ወደእኛ ከሚላኩ ጠላቶች ብንታገሥ ብፁዓን እንደሆንን መነገሩ
    💙ምዕራፍ ፱፡-
    -ፍጥረታት ሁሉ የእግዚአብሔር እንደሆኑና እርሱም እንደሚመግባቸው መነገሩ
    -ነፍሳችን ከሥጋችን ሳትለይ የፈጣሪያችንን የእግዚአብሔርን ፈቃድ እንድንፈጽም
    💙ምዕራፍ ፲፡-
    -ስለትንሣኤ ሙታን መነገሩ
    -ለሰው ጌጡ ንጽሕና፣ ጥበብና ዕውቀት፣ ያለ መቅናትና ያለ ምቀኝነትና መዋደድ እንደሆነ
    -ክፉ ላደረገብህ ሰው ክፉ ነገር አለማድግ እና መታገሥ እንደሚገባ
    💙💙💙የዕለቱ ጥያቄዎች💙💙💙
    ፩. አጋንንት የሚፈሯቸው እነማንን ነው?
    ሀ. ብዙ ገንዘብ ያላቸው ሰዎችን
    ለ. እግዚአብሔርን የሚፈሩ ሰዎችን
    ሐ. ብዙ ምድራዊ ሠራዊት ያላቸውን
    መ. ሀ እና ሐ
    ፪. ከሚከተሉት ውስጥ ትክክል የሆነው የቱ ነው?
    ሀ. የጻድቃን ነፍሳት በመላእክት ይባቤ ደስ ይላቸዋል
    ለ. የኃጥኣንን ነፍሳት አጋንንት ይዘባበቱባቸዋል
    ሐ. ጻድቃን ይህንን ዓለም ስለናቁት ደስ ይላቸዋል
    መ. ሁሉም
    ፫. በእግዚአብሔር ስለሚያምኑ ሰዎች ትክክል የሆነው የቱ ነው?
    ሀ. ፍርሃትና ድንጋጤ የለባቸውም
    ለ. ልቡናቸው የቀና (ቅን) አይደለም
    ሐ. ሰላም የላቸውም
    መ. ለ እና ሐ
    ፬. በመጽሐፈ መቃብያን መሠረት የሰው ጌጥ ከተባሉት መካከል የሆነው የቱ ነው?
    ሀ. ያለመቅናትና ያለምቀኝነት መዋደድ
    ለ. ጥበብና ዕውቀት
    ሐ. ንጽሕና
    መ. ሁሉም

Комментарии • 3