የማቴዎስ ወንጌል ትምህርት 10-ብፁዓን ናቸው(ክፍል 1) በማሙሻ ፈንታ-Matthew Teaching 10-Blessed Are...(Part 1) By Mamusha F
HTML-код
- Опубликовано: 3 мар 2023
- ይህ ትምህርት በኢትዮጵያ የሕይወት ብርሃን ቤተ ክርስቲያን፣ በአዲስ ክርስቲያን ላይፍ አሴምብሊይ አጥቢያ ዘወትር አርብ በማሙሻ ፈንታ እየተዘጋጀ የሚቀርብ ነው።
ትምህርቱን በቀጥታ ስርጭት መከታተል ለምትፈልጉ
ዓርብ ምሽት 11:30 - 1:30
Yoututube - Equip Media / @equipmedia2577
Facebook - Equip Media Mamusha Fenta
/ 312726798871156
አድራሻችን፡ ካዛንቺስ ከመለስ ዜናዊ ፋውንዴሽን ባሻገር 200 ሜትር ገባ ብሎ
ጉግል ማፕስ - google maps address
maps.app.goo.gl/q3YEWmN37C8ec... Развлечения
#እነሆ_ንጉሥሽ
#የማቴዎስ_ወንጌል_ትምህርት_10
#ብፁዓን_ናቸው (ክፍል 1)
#በማሙሻ_ፈንታ
📖 ማቴ 5:1-12
- "የተራራው ስብከት" የሚባሉት ከማቴ 5 - 7 ያሉት ክፍሎች ናቸው።
- በማቴዎስ ወንጌል 5 የተለያዩ ክፍሎች አሉ፤ የመጀመሪያው ይሔ ነው።
- የተራራው ስብከት መነሻው ምዕራፍ 4:23-25 ላይ ነው፤ የኢየሱስ አገልግሎት እጣሬ ነው።
* እያስተማረ
* እየሰበከ
* እየፈወሰ ይዞር ነበር። በዚህ ምክንያት ዝናውም ወጣ፤ ህዝቡም ወደሱ ይጎርፍ ጀመረ። ኢየሱስስ ምን አደረገ? ምዕ 5: 1 ወደ ተራራ ዞር አለ።
- የኢየሱስ ዋና አገልግሎት ማስተማር ነበር። ሁሉ ነገር ወደማስተማር ካልመጣ ኪሳራ ነው። ኢየሱስ ተአምራት ያደርጋል፤ አጋንንት ያወጣል፣ ይፈውሳል ግን ይሔ ሁሉ ወደ ትምህርት ለማምጣት ነው።
- ኢየሱስ ዝም ብሎ ተአምራትን እያደረገ የሚኖር አልነበረም፤ ይሰብክም ነበር።
- እነማንን ነው የተራራውን ስብከት ያስተማራቸው? ቁ.1-2
* ደቀመዛሙርትንም (ተከታዮቹንም፤ ተማሪዎቹንም)
* ሕዝቡንም
📖 ማቴ 7:28 ..ሕዝቡ በትምህርቱ ተገረሙ
- በተራራው ላይ ያስተማረው የመጀመሪያው ሕግጋቱን ነው (ከምዕ 5-7)
- ኢየሱስ ሕግ ፈጻሚ እንጂ አፍራሽ አይደለም። የሕቱ ትርጓሜን ይሰጣል እንጂ አይጥልም።
📖 ማቴ 5:17
* እግዚአብሔር የምግባር ሕግጋቱን አልቀየረም የምንፈጽምበትን ጉልበት ሰጠን እንጂ።
📖 ማቴ 7:14
- የብሉይ ኪዳን ሕግጋት በአዲስ ኪዳን መተርጎም፤ መተንተን፤ መብራራት ስላለባቸው ለሱ ነው የመጣው።
- የተራራው ስብከት ክፍሎች (5-7)
1) ከቁ 3-16 - መግቢያ
2) ከ5:17 - 7:12- ዋናው ትምህርት
3) 7:13 - 27 - ማጠቃለያ
🛑 መግቢያ
* ኢየሱስ ያስተማራቸው ብፅናዎች (3-12)
- ብፁዓእን :- የተባረኩ፣ ደስተኞች፣ እግዚአብሔር የተቀበላቸው፣ በእግዚአብሔር ዘንድ የተወደደ ሕይወት ያላቸው፣ የእግዚአብሔርን ሞገስ ያገኙ ናቸው።
- ለመግባት የሰሩት ሳይሆን ስለተቀበላቸው የሆኑት ባህሪያት ናቸው። እግዚአብሔር መንግስት የገቡ ግን እነዚህን የመሠሉ ባህርያት አላቸው።
- የእግዚአብሔር መንግስት ወደፊት የምንጠባበቃት ብቻ ሳትሆን አሁን የምንገባባት ናት።
- ብፅዕና ሰርተን የምናገኛቸው ሳይሆኑ ወደ እግዚአብሔር ስለገባን ያገኘናቸው ናቸው።
- ብፅዕና ለጥቂት ሰዎች ብቻ የተሰጠ አይደለም። በክርስቶስ በኩል ወደ እግዚአብሔር እንምጣ፤ ክርስቶስን እንቀበል እንጂ ሁላችን ብፁዓን ነን።
- እግዚአብሔር ወደመንግስቱ በኑሮ ምዘና አላስገባንም፤ የገቡ ግን ኑሯቸው ሲመዘን እነዚህ ባህርያት ይገኙባቸዋል።
- የእግዚአብሔር መንግስት በአድርግ አታድርግ አይገባባትም።
- ክርስትና ሲፈተሽ ህይወት አለው፤ ባህርይ አለው። ተደርጎልሀል፤ ሆኖልሀል ብቻ አይደለም የሕይወት ኳሊቲ ይጠይቃል።
- እግዚአብሔር የተቀበላቸው ባህርያት ምንድናቸው?
1) በመንፈስ ድሆች የሆኑ
2) የሚያዝኑ
3) ጽድቅን የሚራቡና የሚጠሙ
- የእግዚአብሔር ሕዝብ ቀጥታ ከእግዚአብሔር ጋር ያላቸውን ግንኙነት የሚያሳዩ ናቸው።
- የመንግሥቱ ሕዝብ መታወቂያዎች ናቸው።
1) የመንፈስ ድህነት ምንድነው ?
- ከባዶነት የጀመረ ህይወት ያላቸው፤ በተሰበረ ልብ ህይወታቸው የጀመረ ናቸው።
- ሰው ቁሳዊ ሀብትና ንብረት ኖሮትም በመንፈስ ድሀ ሊሆን ይችላል። (ማቴ 19)
- ሰው ገንዘብ ፣ ሀብት ንብረት የማይሞላው ማንነት አለው።
- በመንፈስ ድሆች የተሰበረ ልብ ያላቸው፣ ትምክህት የሌላቸው፣ በትህትና ዝቅ ያሉ፣ የተዋረደ መንፈስ ያላቸው፣ በእግዚአብሔር ፊት በትህትና የሚገቡ፣ አልችልም የሚሉ፣ በራሳቸው የማይቆሙ ናቸው።
📖 ሉቃ 48:9-14
- እግዚአብሔር ሊሞላን ሲፈልግ መጀመሪያ ትጥቅ ያስፈታናል።
- የእግዚአብሔር መንግሥት የትምክህት አይደለችም፤ መሞላት የሚፈልጉ ከባዶነት ነው የሚጀምሩት።
- የጸደቀ ሰው ጽድቅን አይጠግብም።
- ለእግዚአብሔር መሠበር ጥሩ ነው። ከእግዚአብሔር ጋር ባለ ግንኙነት ካልተሰበርን አንጠገንም።
- የተባረከ ህይወት በትምክህት አይገኝም፤ በእግዚአብሔር ፊት በትህትና በመሆን እንጂ።
2) የሚያዝኑ
- ሀዘን ቁጭ ብለው ሲቆዝሙ ይውላሉ ማለት አይደለም።
- ክርስትና አለመሳቅ አይደለም፤ ደስታ ነው።
- በራሳቸው ድካም፣ በዙሪያቸው በሚያዮአቸውም ድካም፣ በሀጢአት፣ ስላልዳኑ ሰዎች፣ ያዝናሉ ።
3) የጽድቅ ረሀብና ጥማት
- ጽድቅ፦ ከእግዚአብሔር ጋር ያለ ትክክለኛ ኑሮ ማለት ነው።
- እግዚአብሔር የሚከብርበት ነገር በተመለከተ ሁልጊዜ ረሀብተኛ ናቸው።
- ሁልጊዜ ይጠማሉ አንድ ነገር ላይ አይቆሙም፤ ይበቃኛል አይሉም።
- እውነተኛ የእግዚአብሔርን ነገር መለማመዳችንን የምናውቀው ሁልጊዜ ቀጣዩን እንጠማለን።
ትህትና ይብዛልን
Amen tihwuti nafisi egzaberini yayutali❤@@selamugenetu9253
ክቡር ሁሉ ለልኡል እግዚአብሔር አምላክ ይሁን.. ዶ/ር ማሙሻ እና ዶ/ር አብርሃም እና ሌሎች በዚህ አግልግሎት እያነጻቹን ያላቹ እግዚአብሔር አምላክ አብዝቶ ይባርካቹ ሁላቹሁም ተባረኩልኝ 🙏🏽🔥🔥🔥
አሜን ጌታ ሆይ
ብፅዕና
ተባረኩ
ትውልዳችሁ፡ያተበራካ፡ይሁን።
እግዚአብሔር ይባርካችሁ መላው የዚህች ቤተክርስቲያን አገልጋዮች ።
ዶክተር ማሙሻ ሌሎች ወንድሞችም ጌታ ኢየሱስ ይባርካችሁ ጸጋውን ያብዛላችሁ ።
Amennnnn ዘመናቹ ይለምልም የቃሉ ፍቺ ያበራል አላዋቂን ጠቢባን ያደርጋል ጌታ ልቤን ያብራ
እግዚአብሄር ብርክ ያርጋቹ የተማርነው የምንኖር ያርግልን
እሜን! የሚያዝን: የተጠማ; የተሰበረ ልብ አብዛልን ጌታ ሆይ!!!! ተባረክ ዶክተር ማሙሻ ታንክዩ ❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤
እግዚአብሄር ይባርክህ 👏👏🙏🙏🙏🙏
ጌታ ኢየሱስ አብዝቶ ይባርካችሁ 👏👏🙏
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
Amen amen 🙏 bless you mamush ,👍🙏♥️
Thank you Jesus for brothers who feed
us your precious word.
አሜን ያልገባኝን የማላውቀውን ጌታ በእናንተ አልፎ እያሳወቀኝ .........
ጌታ የሱስ አብዝቶ ይባርካችሁ ፡፡
በምድረ በዳ ሆኖ ጌታን መጠማት ምንም በሌለበት ተስፋ በሚያስቆርጥ ስፍራ የውሀ ጥም በሚያንገላታበት ስፍራ እግዚአብሔርን መንፈስ መጠማት የመንፈስ ድሀ መሆን ጌታ ይጨምርልኝ ተባረክ ዶር ማሙሻ የሚያስተምር መንፈስ ቅዱስ ስሙ ብሩክ ይሁን
Amen amen
geta yibarkrk
የምወደው ከስወች ጋር ያለኝ ግንኙነት ትክክል ሳይመስለኝ ሲቀርና ዝለት ሲመጣብኝ ሮጨ የማነበው ማቴዎስ 5-7 ይህን ክፍል ከጀመርኩ መውጣት ይቸግረኛል ምክኒያቱም ራሴን በዛ ውስጥ አየዋለሁና ።
Stay blessed our dear brother!
God bless you more and more
ዘመናችሁ ይባረክ በዚህ አገልግሎት የተሳተፋችሁ ሁሉ በጣም እየተጠቀምኩ ነዉ ጌታ ይባርካችሁ;:☺😊
ጌታ ይባርካችሁ አገልግሎታችሁ ይባርክ። እባካችሁ ጊታሩ ለይ ያለው ባንዲራ ያለ ማሰተዎል ይመስለኛል የዘመኑን ሬንቦ ይመስላልነ አንሱት ጠላት በብዙ እየሰራ ያለበት ዘመን ስለሆነ እነስተውል ባንዲራውን ሌላ ቦታ ብታደርጉት መልካም ነው። ተባረኩ
ጌታ የሱስ ክርስቶስ ይባርካችሁ እኔ ይህን ቭደው እየተከታተልኩ ብዙ ተጠቃም ሆኛለሁ ጌታ በመንፈሱ ከእናንተ ጋር ይሁን፡፡
አሜን🙏🏾
Good bless you Dr Mamusha ur our blessing
ዶ/ር ማሙሻ ተባረክ ለበረከት ሁን
ማሙሻ ኑርልን 👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏
AMEN AMEN GETA HOY ERDAN🙏🙏🙏🙏
የሚገርም የህይወት መመሪያ ነዉ። ተባርካሀል ዶክተር ማሙሻ።
Thankyou D/r you is Righteous really the kingdom preachers!!!
Amenn.Amennn.aba ameseginhalehu🙏🙏🙏 dr mamusha tebarek
ዘመንህ ይባረክ!!!
Amen Pastor ስትሄዱ እንዳትረሱኝ። በጣም ጥሩ ሃሳብ ነው ። እግዚአብሔር ይረዳናል።
ተባረክ ዶ/ር ማሙሻ ጌታ ይባርካችሁ፡፡
ዶ/ር ማሙሻ እግዚያብሔር ይባርክህ። አብረውክም ተጠምደው የእግዚአብሔርን ስራ የሚሠሩ ሁሉ ይባረኩ።
Egziabiher Amlak ybarkh Doctor mamush.
Dr Mamusha I missed you God bless you
Geta yimesgen
የኢትዮጵያ ወጣቶች ይህም አይነት ኢትዮጵያውያን እንዳሉ እወቁ ኩሩ ተከተሉ ተስተካከሉ። እኛ የምናእቃት ኢትዮጵያ ፣ በየአለሙ የምንሰፈሰፍላት ኢትዮጵያ ይህች ናትና፣ ጠብቁአት አክብሩአት፣ ዞሮ መግቢያችን ኢትዮጵያ ይህች ናት።
ጊታሩ ላይ ያለው አርማ ሌላ ነገር ይመስላል እባካቹ ነገር ለሚቆረቁሩ ጥሩ መስሎ አልታየኝም የጌዎች ባንዲራ ሊመስል ይሄዳል ፕሊስ ቅዱሳን ጥንቃቄ
እኔም መስሎኛል 😮😮
ትህትና የልብ ሀሳብ /motive /ነው እንጂ መቅለስለስ አይደለም ጮክ ብሎ በድፍረት መናገር ትህትና አይደለም ልንል አንችልም በተለይ እኛ ሀገር የትህትና ትርጉም የተሳሳተ ነው። እ/ር ናችሁ ያለንን ነን ማለት ትእቢት አይደም