ፊላደልፊያ ክፍል 2 | ሰባቱ አብያተክርስቲያናት | ፓስተር አስፋው በቀለ | www.operationezra.com
HTML-код
- Опубликовано: 12 окт 2024
- ፊልድልፍያ፡ በስደት የጸናች ቤተ ክርስቲያን (ራእይ 3፡7-13)። የፊልድልፍያ ከተማ በጠንካራ ግንብ የታጠረችና መልካም ኢንዱስትሪ የነበራት ሲሆን፥ ከተማይቱን አቋርጦ የሚያልፍ ጠቃሚ ጎዳና ነበር። ብዙውን ጊዜ ግን የመሬት መንቀጥቀጥ ይነሣባት ነበር። ከዚህም የተነሣ ብዙ ሰዎች ከከተማይቱ ውጭ ይኖሩ ነበር። ይህም የነዋሪዎቿን ቁጥር አመነመነው። ዮሐንስ ይህን መልእክት በሚጽፍበት ጊዜ የፊልድልፍያ ቤተ ክርስቲያን አሁንም ጥቂት ምእመናን ብቻ ነበሯት። ነገር ግን እግዚአብሔር የሕዝብን ብዛት እንደ ዋነኛ በረከት አይቆጥረውም። እርሱን በበለጠ የሚያሳስበው ታማኝነታችን ነው። የፊልድልፍያን ቤተ ክርስቲያን ከደረሰባት ስደት ባሻገር ለክርስቶስ ጸንታ የቆመች ነበረች። በመሆኑም ክርስቶስ ለዚህች ቤተ ክርስቲያን ምንም ዓይነት ተግሣጽ ሊሰነዝር አንመለከትም። ይልቁንም ክርስቶስ ማንም ሊዘጋው የማይችል የአገልግሎት በር እንደሚሰጣቸው ቃል ይገባል። በባለሥልጣናት ፊት የሚከራከሯቸው የማያምኑ አይሁዶች እንኳን ሊዘጉባቸው አይችሉም ነበር። ክርስቶስ አይሁዶችን “የሰይጣን ምኩራብ” ሲል ጠርቷቸዋል። ምክንያቱም የሰይጣን መሣሪያዎች ሆነው በአማኞች ላይ ስደትን ያመጡ ነበር። እንዲያውም፥ ክርስቶስ አንድ ቀን አይሁዶች ክርስቲያኖችን ለማክበር እንደሚገደዱ ይናገራል። ከብዙ አሥርተ ዓመት በኋላ፥ በአንድ ዝነኛ ሰባኪ ወይንም ነቢይ አገልግሎት ይህቺ ቤተ ክርስቲያን በከፍተኛ ደረጃ አደገች። እስልምና የአገሪቱን አካባቢ ከወረረ በኋላ ሳይቀር ይህቺ ቤተ ክርስቲያን ለቀጣይ 500 ዓመታት በክርስቶስ ላይ ያላትን እምነት ለመያዝ በቅታለች።
ክርስቶስ በተጨማሪም ለዚህች ቤተ ክርስቲያን “ምድር ላይ የሚኖሩትን ይፈትናቸው ዘንድ በዓለም ሁሉ ላይ ሊመጣ ካለው ከመከራው ሰዓት እጠብቅሃለሁ” የሚል የተስፋ ቃል ሰጥቷል። ክርስቶስ ከፈተናው ሰዓት እጠብቅሃለሁ ሲል ምን ማለቱ እንደሆነ ምሁራን የተለያየ ሐሳብ ያቀርባሉ። በመጀመሪያ፥ እግዚአብሔር ክርስቲያኖች የፈተናውን ሰዓት እንዳይጋፈጡ የሚጠብቃቸው መሆኑን ያሳያል። ሁለተኛ፥ በፈተናው ውስጥ ጉዳት ሳይደርስባቸው እንደሚያልፉ ቃል መግባቱ ነው። ክርስቲያኖች ይህን የተስፋ ቃል በሚተረጉሙበት መንገድ የተለያየ አቋም አላቸው። በመጀመሪያ፥ አንዳንድ አማኞች ክርስቶስ ዮሐንስ ይህን መልእክት ከጻፈ በኋላ በሮም ግዛት ውስጥ በሚገኙ ክርስቲያኖች ሁሉ ላይ ሊመጣ ስላለው የስደት ማዕበል መናገሩ ነው ይላሉ። ክርስቶስ የዚህች ቤተ ክርስቲያን አማኞች በእምነታቸው ምክንያት ከስደቱ እንደሚጠበቁ ቃል መግባቱ ነው ይላሉ። ሁለተኛ፥ ሌሎች ክርስቲያኖች ይህ አማኞች በራእይ 6-19 ውስጥ ለተገለጠው ታላቁ መከራ መፈተን ሳይኖርባቸው ወደ ላይ የሚነጠቁ መሆናቸውን ያመለክታል ይላሉ። ይህ ጥቅስ ብቻ ክርስቲያኖች ከታላቁ መከራ በፊት የሚነጠቁ መሆናቸውን አያረጋግጥም። ክርስቶስ በታማኝነት ጸንቶ ለሚቆም ሰው አያሌ የተስፋ ቃሎችን ሰጥቷቸዋል።
ሀ) በአምላኬ መቅደስ አምድ እንዲሆን አደርገዋለሁ። በፊልድልፍያ ብዙውን ጊዜ የመሬት መንቀጥቀጥ ተነሥቶ ካለፈ በኋላ የሚቀሩት የቤተ መቅደስ አምዶች ብቻ ነበሩ። ስለሆነም ክርስቶስ በዘላለማዊ መንግሥቱ ውስጥ ታማኝ ክርስቲያኖች ማንም የማይወስድባቸውና ከቶውንም የማይነቃነቅ የክብር ስፍራ እንዳላቸው ቃል መግባቱ ይሆናል። ወይም ደግሞ አንዳንድ ሀብታም ሰዎች በቤተ መቅደስ አምድ ጨምረው ስማቸውን በዚያው አምድ ላይ ያሰፍሩና ታላቅነታቸውን ያሳዩ ነበሩ። ክርስቶስ ከስደት ሁሉ ባሻገር ለእርሱ ጸንተው የሚኖሩትን በሰማይ የተለየ ክብር እንደሚያገኙ መግለጹ ይሆናል።
ለ) ክርስቶስ የአብን፥ የአዲሲቱን ኢየሩሳሌምንና አዲስ ስሙን በግለሰቡ ላይ ይጽፋል። በመንግሥተ ሰማይ ታማኝ ሆኖ የሚጸና በእግዚአብሔር ፊት ይከበራል። የእግዚአብሔርና የኢየሩሳሌም ስም የሚጻፍበት መሆኑ ምናልባትም አማኙ የእግዚአብሔር ልዩ ንብረት ሆኖ የአዲሲቱን ኢየሩሳሌም ዜግነት እንደሚያገኝ የሚያመለክት ይሆናል። አዲሱ ስም አማኙ በመንግሥተ ሰማይ በእግዚአብሔር ፊት የሚኖረውን አዲስ ግንኙነት ሊያመለክት ይችላል። አማኞች በምድር ላይ ሊናቁ ቢችሉም፥ በሰማይ ላይ ግን ታማኞች ሆነው ከተገኙ በእግዚአብሔር ዘንድ ይከብራሉ። - Развлечения
አሜን ማራናታ ጌታ እየሱስ ሆይ ቶሎ ና ሙሽራችን እየሱስ ናፍቆታችን ና በቶሎ ቅዱስ እግዚአብሔር ሆይ ስምህ የተባረከ ይሁን ስለ ቅዱስ ቃልህ ስለ ባሪያህ ክብር ላንተ ይሁን ክብርህ ፀጋና ሞገስህ በባሪያህ ላይ ይሁን ዘመኑን ኑሮውን ቤተሰቡን ሁሉ ባርክ።
ፓስተር. ዘበንህን. ያባርክ. ተባርክ. በእውነት. እሁንም. ፀጋው. ያበዛልህ. እያምግብክን. ስላልው. ምግብ
Tebarek bebzu
Glory to God I want to be
Thank you blessings for you and your family
Amen amen thank you
Amen God bless you
Amen amen
Pastor Asfaw God bills you so much
Amen God blessed you more and more 🙏🙏🙏
❤❤❤
አሜን ይመጣል ማራናታ
Amen God blessed you more and more 🙏🙏🙏
God Bless You Pastor
አሜን ፓስተር ተባረክ
ስጦታዬ ነህ ❤❤
አሜን አሜን ማረናታ ጌታ እዬሱስ ክረስቶስ ሆይ ቶሎ ና ሰለም ለአንቴ ይሁን ጰስቴረ አስፈው እግዝአብሄረ ፀገውን ይጨምረልህ በብዙ ፀገ ተበረክ አመኑኤል እግዝአብሔረ ከንቴ ገረ ይሁን ሰለ ከበረው የጌታ ቀል ክብረ ምስገና ታጠቅልሎ ለናገስታት ንጉስ ለአልፈ ኦሜገ ለእግዝአብሔረ ይሁን
Amen Maranata
Geta yebarkeh bebezu
Amen Geta Yibarkeh Pastor
Pastor tebark 'AMLAKE' sil min maletu new eyesus erasu amlak silehon
paster tebarek !ወዴትና የት እንደነበርኩኝ
እንደእነዚህ አይነት ትምህርት ነበር እንዴ .
paster ውሰጤ የናፈቀው ይህንን ነበር ማለት ነው
ማቆም አቃተኘ እኮ ትምህርትህን ይኼኮ ከጌታ የተሠጠኸን መጋቢ ነህ በእወነት እግዚአብሔር ዘመንህን ቤተሰብህን ይባርክ በደሙ የሠውርህ
Amen amen amen maranata
አሜን ይውንልኝ
God bless you
ተባረክ
Ownt naw yegzabeher sew geta yekr yebln
Amen 🙏
Ameeen Ameeem
ፓስተር ዮሐ 3፡10 "በምድር የሚኖሩትን ይፈትናቸው ዘንድ በዓለም ሊመጣ ካለው ከፈተናው ስዓት እጠብቅሀለሁ።" ሲል እኛ ሳንነጠቅ ያለው መከራ አሁን የምናልፍበትን እንጂ የ 7 ዐመቱ ላይ የተዘጋጀን ክርስቲያኖች አንገኝም አይደል?
amane
Amen amen abate yikr belegni in Jesuse name
Amen Amen Amen pastor geta eyesus yebarki yesfah, be timirtu bexam texekemlew power point ena leloch reference beze email dinkudagu@gmail.com attach betaderglegn elalew
ፓሰተር ትናንት እሜሌን ልኬ ነበረ?
ራእይ 3
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³ እንግዲህ እንዴት እንደ ተቀበልህና እንደ ሰማህ አስብ፥ ጠብቀውም ንስሐም ግባ። እንግዲያስ ባትነቃ እንደ ሌባ እመጣብሃለሁ በማናቸውም ሰዓት እንድመጣብህ ከቶ አታውቅም።
⁴ ነገር ግን ልብሳቸውን ያላረከሱ በሰርዴስ ጥቂት ሰዎች ከአንተ ጋር አሉ፥ የተገባቸውም ስለ ሆኑ ነጭ ልብስ ለብሰው ከእኔ ጋር ይሄዳሉ።
⁵ ድል የነሣው እንዲሁ በነጭ ልብስ ይጐናጸፋል፥ ስሙንም ከሕይወት መጽሐፍ አልደመስስም፥ በአባቴና በመላእክቱም ፊት ለስሙ እመሰክርለታለሁ።
⁶ መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚለውን ጆሮ ያለው ይስማ።
⁷ በፊልድልፍያም ወዳለው ወደ ቤተ ክርስቲያን መልአክ እንዲህ ብለህ ጻፍ፦ የዳዊት መክፈቻ ያለው፤ የሚከፍት፥ የሚዘጋም የሌለ፤ የሚዘጋ፥ የሚከፍትም የሌለ፤ ቅዱስና እውነተኛ የሆነው እርሱ እንዲህ ይላል።
⁸ ሥራህን አውቃለሁ፤ እነሆ፥ በአንተ ፊት የተከፈተ በር ሰጥቼአለሁ ማንምም ሊዘጋው አይችልም፤ ኃይልህ ምንም ትንሽ ቢሆን ቃሌን ጠብቀሃልና፥ ስሜንም አልካድህምና።
⁹ እነሆ፥ አይሁድ ሳይሆኑ፦ አይሁድ ነን ከሚሉ ነገር ግን ከሚዋሹ ከሰይጣን ማኅበር አንዳንዶችን እሰጥሃለሁ እነሆ፥ መጥተው በእግሮችህ ፊት ይሰግዱ ዘንድ እኔም እንደ ወደድሁህ ያውቁ ዘንድ አደርጋቸዋለሁ።
¹⁰ የትዕግሥቴን ቃል ስለ ጠበቅህ እኔ ደግሞ በምድር የሚኖሩትን ይፈትናቸው ዘንድ በዓለም ሁሉ ላይ ሊመጣ ካለው ከፈተናው ሰዓት እጠብቅሃለሁ።
¹¹ እነሆ፥ ቶሎ ብዬ እመጣለሁ፤ ማንም አክሊልህን እንዳይወስድብህ ያለህን አጽንተህ ያዝ።
¹² ድል የነሣው በአምላኬ መቅደስ ዓምድ እንዲሆን አደርገዋለሁ፥ ወደ ፊትም ከዚያ ከቶ አይወጣም፤ የአምላኬን ስምና የአምላኬን ከተማ ስም፥ ማለት ከሰማይ ከአምላኬ ዘንድ የምትወርደውን አዲሲቱን ኢየሩሳሌምን፥ አዲሱንም ስሜን በእርሱ ላይ እጽፋለሁ።
¹³ መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚለውን ጆሮ ያለው ይስማ።
anane
Bruk
God bless u Pastor
አሜን ፓስተር ተባረክ
amane
amane
aman