የትውልደ ኢትዮጵያውያን ብቸኛ ደብር በሚልዋኪ ቅኝት

Поделиться
HTML-код
  • Опубликовано: 15 окт 2024
  • የሚልዋኪ ከተማ ትውልደ ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራዊያን መኖሪያቸው ካደረጓቸው የማዕከላዊ ምዕራብ ዩናይትድ ስቴትስ ከተሞች መካከል አንዷ ናት።
    ለእነዚህ ማኅበረሰቦች ትብብር እና ወንድማማችነት እየሠሩ ከሚገኙት መካከል የከተማው ብቸኛ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ን ደብረ ጽዮን ቅድስት ልደታ ለማሪያም ትገኝበታለች።
    ከትውልድ ሀገራቸው ርቀው ለሚኖሩት ኢትዮጵያን እና ኤርትራዊያን በዋነኝነት መንፈሳዊ አገልግሎት ለመስጠት የተቋቋመችው ቤተክርስቲያን፣ ከዚህ ተሻግራ ወጣቶች ስለ ባህል እና ማንነታቸው እንዲያውቁ ፣ በቀለም ትምህርት እንዲበረቱ የሚያግዙ መርሀ ግብሮችን ዘርግታለች።

Комментарии •