አባ መቃርስ - ክፍል - 1 / Aba Mekars Part - 1 Ye Kidusan Tarik

Поделиться
HTML-код
  • Опубликовано: 8 фев 2025
  • ታላቁ ቅዱስ መቃርስ
    ታላቁ ቅዱስ መቃርስ ወይም ቅዱስ መቃሬ 'ጽድቅ እንደ
    መቃርስ' የተባለለት: የመነኮሳት ሁሉ አለቃ: ከ80 ዓመታት
    በላይ በበርሃ የኖረ: በግብፅ ትልቁን ገዳም ወይም አስቄጥስን
    የመሠረተ: ከ50,000 በላይ መነኮሳትን ይመራና
    ይመግብ የነበረ ፍፁም ጻድቅ ነው::
    በ4ኛው መቶ ክ ዘመን አርዮሳውያን ደጉን ታላቅ አባት
    በሰንሰለት አስረው ከግብፅ ወደ እስያ በርሃ ከጉዋደኛው
    ቅዱስ መቃርዮስ እስክንድርያዊ ጋር አሰድደውታል:: በዚያ
    ለ2 ዓመታት ስቃይን ከተቀበሉ በሁዋላ በአረማውያን ፊት
    ድንቅ ተአምር አድርገው አረማውያንን ከነንጉሳቸው
    አጥምቀዋል::
    በተሰደዱባት ሃገርም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም
    አጠራሩ ይክበርና እመቤታችንን: ቅዱሳን ሐዋርያትን:
    አዕላፍ መላእክትን: በተለይ ደግሞ ቅዱሳኑን ዳዊትን:
    ዮሐንስ መጥምቁንና ወንጌላዊውን: ማርቆስን: ዼጥሮስን:
    ዻውሎስን አስከትሎ ወርዶ ተገልጦላቸዋል:: በቅዱስ
    አንደበቱም የምሕረት ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል::
    ታላቁ ቅዱስ መቃርስና ባልንጀራው መቃርዮስ ከ2
    ዓመታት ስደትና መከራ በሁዋላ ስደት በወጡባት ዕለት
    መልዐኩ ኪሩብ በክንፉ ተሽክሞ ወደ ግብፅ
    መልሷቸዋል:: በወቅቱም ጻድቁን ለመቀበል ከ50,000
    በላይ የሚሆኑ ልጆቻቸው መነኮሳት በዝማሬ ወጥተዋል::
    ስለ ታላቁ ቅዱስ መቃርዮስ ቅድስና ለመጻፍ መነሳት
    በረከቱ ብዙ ነው:: ግን 'ዓባይን በጭልፋ' እንዲሉ አበው
    ከብዛቱ የተነሳ የሚዘለቅ አይሆንም::
    ቅዱስ መቃርስ ከዘመናት በላይ በቆየበት የበርሃ
    ሕይወቱ:-
    1.አባ ብሶይ: አባ ባይሞይ: አባ ሳሙኤል: አባ በብኑዳን
    ጨምሮ እርሱን የመሰሉ ወይም ያከሉ ቅዱሳንን ወልዷል::
    2.ለሕይወታችን መንገድ የሚሆኑንን ብዙ ቃላትን
    ተናግሯል::
    3.ከገዳማት እየወጣ በብዙ ቦታዎች ቅዱስ ወንጌልን
    ሰብኩዋል::
    4.አጋንንትን ድል ከመንሳት አልፎ እንደ ባሪያ ገዝቷቸዋል::
    5.ለዓይንና ጀሮ ድንቅ የሆኑ ብዙ ተአምራትን ሰርቷል::
    በእነዚህና ሌሎች ምክንያቶችም ቤተ ክርስቲያን "ርዕሰ
    መነኮሳት ወይም የመነኮሳት ሁሉ አለቃ" ስትል ትጠራዋለች::
    በ97 ዓመቱ መጋቢት 27 ቀን ሲያርፍ መላእክት ብቻ
    ሳይሆን አጋንንትም ስለ ድል አድራጊነቱ ዘምረውለታል::
    ታላቁ ቅዱስ መቃርስ ካረፈ በሁዋላ ከክቡር ሥጋው
    ብዙ ተአምራት ይታዩ ነበርና የሃገሩ ወይም የሳስዊር ሰዎች
    ሊወስዱት ፈለጉ:: ሳስዊር ማለት ቅዱሱ ተወልዶ
    ያደገባት: ወላጆቹ ወይም አብርሃምና ሣራ ይባላሉ የኖሩባት ቦታ
    ናት:: የምትገኘውም ግብጽ ውስጥ ነው::
    በምድረ ግብጽ: በተለይም በገዳመ አስቄጥስ የአባ
    መቃርስን ያህል ክቡርና ተወዳጅ የለምና የሃገሩ ሰዎች
    የነበራቸው አማራጭ መስረቅ ነበር:: መሥረቅ ኃጢአት
    ቢሆንም እነሱ ግን ስለ ፍቅር: አንድም ለበረከት ወይም በረከትን
    ሲሹ አደረጉት::
    ወደ ሳስዊርም ወስደው: ቤተ ክርስቲያን በቅዱሱ ስም
    አንጸው በክብር አኖሩት:: በዚያም ለ160 ዓመታት
    ተቀመጠ:: በ7ኛው መቶ ክ-ዘመን ግን ተንባላት
    ወይም እስላሞች መጥተው ቤተ ክርስቲያኑን አጠቁ:: በዚህ
    ጊዜም ሕዝቡ የጻድቁን አጽም ይዘው ሸሹ:: በሌላ ቦታም
    እንደ ገና በስሙ ቤተ ክርስቲያን አንጸው በዚያ አኖሩት::
    በእነዚህ ሁሉ ዓመታት የመንፈሳዊ አባታቸውን ሥጋ
    ያጡት የገዳመ አስቄጥስ ቅዱሳን ያዝኑ ይጸልዩ ነበርና
    ልመናቸውን ፈጣሪ ሰማ:: አባ ሚካኤል ሊቀ ዻዻሳት
    በነበረበት ዘመን: ከገዳሙ ለሌላ ተግባር ወደ ሳስዊር
    የተላኩ አበው ከታላቁ አባት ቤተ ክርስቲያን ሲደርሱ
    ሰውነታቸው ታወከ::
    ይዘው ለመውሰድ ሙከራ ቢያደርጉ ሊሳካላቸው
    አልቻለም:: ምክንያቱም የቤተ ክርስቲያኑ ጠባቂ ደወል
    ደውሎ ሕዝቡን ሁሉ ጠርቶ ነበርና:: ሕዝቡና ሃገረ ገዢው
    የሆነውን ሲሰሙ "የቅዱሱን ሥጋ ብትነኩ እንገላቹሃለን"
    ብለው ሰይፍ: ዱላ: ጐመድና ጦር ይዘው መጡባቸው::
    መነኮሳቱ ግን ባዷቸውን ሊመለሱ አልፈቀዱምና ሌሊቱን
    ሲያለቅሱና ሲጸልዩ አደሩ:: መንፈቀ ሌሊት በሆነ ጊዜም
    ታላቁ መቃርስ በግርማ ወርዶ መኮንኑን "ለምን ወደ ልጆቼ
    እንዳልሔድ ትከለክለኛለህ?" ሲል በራዕይ ተቆጣው::
    በዚህ ምክንያትም መነኮሳቱ የቅዱሱን ሥጋ ተቀበሉ::
    ሕዝቡም በዝማሬና በማሕኅሌት: ከብዙ እንባ ጋር
    ሸኟቸው:: ታላቁ መቃሬ ወደ ገዳሙ ሲደርስም ታላቅ ደስታ
    ተደረገ:: ቅዱሳን ልጆቹ ከመንፈሳዊ አባታቸው ተባርከው
    በክብር አኑረውታል::
    አምላከ ቅዱሳን የታላቁ ቅዱስ መቃርስን ትሕትናውን:
    ትእግስቱንና ቅንነቱን ያድለን:: በበረከቱም ይባርከን::
    ምንጭ ››› " ዝክረ ቅዱሳን Saints Of The Orthodox Church " የፌስቡክ ገፅ - www.facebook.c...
    ይህን መንፈሳዊ ፊልም አዘጋጅተውና ተርጉመው ላቀረቡልን ቃለ ሕይወት ያሰማልን፡፡

Комментарии • 817