ኢየሱስ "እኔ ነኝ" ነው (የእግዚአብሔር ልጅ - ክፍል 20)
HTML-код
- Опубликовано: 13 сен 2024
- እግዚአብሔር በሚነድደው ቍጥቋጦ ውስጥ ለሙሴ ተገልጦ ለመጀመሪያ ጊዜ ስሙን ያሳወቀበትን ትራኬ እናስቀድም። ሙሴ፣ “ወደ እስራኤል ሕዝብ ሄጄ ‘የቀድሞ አባቶቻችሁ አምላክ ወደ እናንተ ልኮኛል’ በምላቸው ጊዜ እነርሱ ‘ስሙ ማን ነው?’ ብለው ቢጠይቁኝ ምን እመልስላቸዋለሁ?” የሚል ጥያቄ አቅርቦ ነበር። እግዚአብሔርም፣ “እኔ ‘ያለሁና የምኖር ነኝ፤’ ስለዚህም ‘እኔ ነኝ’ ወደ እናንተ ልኮኛል በላቸው” የሚል ምላሽ ሰጥቶታል (ዘፀ. 3፥13-14፤ አት)። በዚህ ምንባብ ውስጥ “ያለሁ፣ የምኖር፣ እኔ ነኝ” በሚል በሦስት መልኩ የተተረጐመው “ኤህዬህ (אֶהְֽיהֶ)” የሚለው የዕብራይስጥ ቃል ነው። የግሪክኛው ብሉይ ኪዳን (ሰብዓ ሊቃናት) እግዚአብሔር በዚህ ስፍራ ራሱን ያስተዋወቀው “ኤጎ ኤሚ ሆ ኦን” (ἐγώ ειμι ο ων) በማለት እንደ ሆነ ይገልጣል። ይህም በበርካታ የእንግሊዝኛ ትርጕሞች “I AM WHO I AM” ተብሎ ተተርጕሟል። “እኔ ብቻዬን እኔ እንደ ሆንሁ (በግሪክኛው ኤጎ ኤሚ)፣ ከእኔም በቀር አምላክ እንደሌለ እዩ” የሚለው ዘዳግም 32፥39ም ከዚሁ ጋር ይስማማል። ጌታ ኢየሱስ “እኔ ነኝ” ሲል እነዚህን ታሳቢ ያደረገ ስለ መሆኑ ቀጥለን እንመለከታለን።
You are blessed brother. “ቃልህ ለጕሮሮዬ ጣፋጭ ነው፤ ከማርና ከወለላ ይልቅ ለአፌ ጣፈጠኝ።” መዝሙረ ዳዊት 119:103
ብቻውን ለሆነ አምላክና መድኃኒታችን ከዘመን ሁሉ በፊት አሁንም እስከ ዘላለምም ድረስ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ክብርና ግርማ ኃይልም ሥልጣንም ይሁን፤ አሜን።
አሜን
እንኻን ለአዲስ ዓመት በሠላም ጌታ አደረሰህ ።እጅግ መልካም ትምህርት ነዉ ።በርታ የምከትዬሽ ትምህርት ጭምር ነው ።መሠረት መያዝ የሚያስችል ትምህርት ነዉ
እግዚአብሔር ይስጥልኝ
ተባረክ
Amen
ወንድሜ ተባረክልኝ ።
አሜን
Many blessings Paulos and happy Ethiopian new year!
God bless you Kidi
መልካም አዲስ አመት
ለሁላችንም
እኔ ጋር ድምጽ አለው
Thanks
Ere sewoch ene bicha negn Weis hulum gar new የእግዚአብሔር ልጅ yemilew 20ውም ክፍል ድምጽ የለውም min baderg yishalegnal chigiru mindinew
ችግሩ አንተ ጋ ነው። ጥሩ ድምፅ አለው
@@PaulosFekaduo thanks be earphone yiseral eyesemaw new tnx be blessed ❤️❤️❤️❤️🙏❤️🙏❤️